Thursday, September 27, 2018

“ኤዎስጣቴዎስ ከፋሌ ባሕር”

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ!

አንተ ት(ኮ)ንን ኃይለ ባሕር---ውቅያኖስን የምትገዛ አንተ ነህ ፤ ወአንተ ታረምሞ ለድምፀ ማዕበላ---እስከ ዝየ ብጽሒ ብለህ የውቅያኖስን ማዕበል ሞገዷን ፀጥ የምታደርገው አንተ ነህ ፡፡  አንተ አኅሠርኮ ለዕቡይ ከመ ቅቱል--- ሌዋታንን እንደሞተ ያዋረድከው አንተ ነህ ማለት በባሕር ተወስኖ እንዲኖር  ያደረግኸው  አንተ ነህ”   መዝ   88፥ 9-10
============================================

Wednesday, September 26, 2018

“ፍልሰተ ሥጋሁ ለቅዱስ እስጢፋኖስ ወአባ ጴጥሮስ”

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ
“ፍልሰተ ሥጋሁ ለቅዱስ እስጢፋኖስ ወአባ ጴጥሮስ”
========================

አመ  አሥሩ ወሐሙሱ ለመስከረም በዛቲ ዕለት ኮነት ፍልሰተ ሥጋሁ ለቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት ወቀዳሜ ሰማዕት--መስከረም አሥራ አምስት በዚህች ቀን  የዲያቆናት አለቃና የሰማዕታት መጀመሪያ ለሆነ ለቅዱስ እስጢፋኖስ ፍልሰተ ሥጋው ሆነ ፡፡ ይህም እንዲህ ነው ከአረፈበት ጊዜ ብዙ ዓመታት ካለፉ በኋላ ሦስት መቶ ዓመታ ያህል ከዚህም በሚበዛ ዘመን ጻድቁ ቈስጠንጢኖስ ሲነግሥ ፤ የቀናች ሃይማኖት ተገልጣ የሕያው የእግዚአብሔር አምልኮት በሁሉ ሲዘረጋ ያን ጊዜ የቅዱስ እስጢፋኖስ ሥጋ በአለበት አቅራቢያ የገማልያል ቦታ በምትባል በኢየሩሳሌም በአንዲት ቦታ ሰው ይኖር ነበር ፡፡የዚያ ሰው ስም ሎክያኖስ ይባል ነበር ፡፡

Saturday, September 22, 2018

እንጠያየቅ ክፍል 2


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ

ይድረስ ለሰሚጆሮና ለአስተዋይ እዝነ ልቡና
============================


የዚህ ጽሑፍ ተከታታይ ወንድም እህቶቼ እንደምን ቆያችሁልኝ?ሕይወት?ጤና?ሥራ?መልካም እነሆም ለዛሬዉ ደግሞ የእንጠያየቅ ዘዉግ የሚያተኩረዉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዉስጥ ነገረ ቅብዐት ሲነሳ ብዙዎቻችሁ እንግዳ ፣ ዘላን ምድረ በዳ ትሆኑበታላችሁና መጻሕፍት ስለተቀብዐ ምን ይላሉ የሚለዉን ይሆናል ፡፡ እናንተ “ተዋሕዶዎች” ግን እኮ መጽሐፍ “እናንተስ ከቅዱስ ቅብዓት ተቀብታችኋልና ሁሉን ታዉቃላችሁ” 1ኛ ዮሐ 2 ፡ 20 ተብሎ ተነግሯል ፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ

እንጠያየቅ ክፍል ፪

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ
እንጠያየቅ ክፍል ፪
ይድረስ ለሰሚጆሮና ለአስተዋይ እዝነ ልቡና
========================


የዚህ ጽሑፍ ተከታታይ ወንድም እህቶቼ እንደምን ቆያችሁልኝ?ሕይወት?ጤና?ሥራ?መልካም እነሆም ለዛሬዉ ደግሞ የእንጠያየቅ ዘዉግ የሚያተኩረዉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዉስጥ ነገረ ቅብዐት ሲነሳ ብዙዎቻችሁ እንግዳ ፣ ዘላን ምድረ በዳ ትሆኑበታላችሁና መጻሕፍት ስለተቀብዐ ምን ይላሉ የሚለዉን ይሆናል ፡፡ እናንተ “ተዋሕዶዎች” ግን እኮ መጽሐፍ “እናንተስ ከቅዱስ ቅብዓት ተቀብታችኋልና ሁሉን ታዉቃላችሁ” 1ኛ ዮሐ 2 ፡ 20 ተብሎ ተነግሯል ፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ 

ፈለገ ጥበብ መፅሔት ዘየኔታ ገ/ስ አወቀ - ልደተ ክርስቶስ በዘመነ ዮሐንስ

ልደተ ክርስቶስ በዘመነ ዮሐንስ - ከየኔታ ገ/ስላሴ አወቀ የአራቱ ጉባኤያት መ/ር  (መግረሬ ፀር በሚለው አምድ ስር ያለውን ያንብቡት)

ስለ እኛ

ምስጢረ ቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ
 ከብራና ወደ ወረቀት የተቀየሩ የቅዱሳን አበው መጽሐፍት [ስርዋጽም የተጨመረባቸውም ብዙዎች አሉ]

ቅዱሳን አበውን "የኑሮአቸውን ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነት ምሰሏቸው" ዕብ ፲፫፥፯  ብሎ ሐዋርያው  ቅዱስ ጳውሎስ  እንዳስተማረን  እኛም  እነርሱን አብነት አድርገን ትንቢታቸውን፣ ስብከታቸውን፣  ድርሳናቸው፣  ገድላቸውን ተቀብለን ለዘመናት  ኖረናል እየኖርንም  እንገኛለን ::

ነገር  ግን በቀደሙት ሐዋርያትና  በሊቃውንት እግር  የተተኩት የዘመናችን  መምህራን ቅዱሳን አበው  የተናገሩትን ትክክል አይደለም በማለት የራሳቸውን ሀሳብ እየጨመሩ [ስርዋጽ -አዲስ ነገር እያስገቡ]ና የነበረውን  ደግሞ እያስወጡ  በማር የተለወሰ መርዝ  በኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ  ቤተ ክርስቲያን ላይ እየዘሩ ይገኛሉ::

 ነገርግን እኛ ይህንን በመረዳት ለምን እንዲህ ታደርጋላችሁ ብለን ብንጠይቅም ምላሽ ስላልተገኘ እያንዳንዷን ጉዳቸውን ከቀደሙት አበው መጽሐፍት እያወጣን እንዴት እንዳወጡትና እንደጨመሩበት በግልጽ ለመወያየት ይህንን ጦማር መፍጠር አስፈላጊ ሆኖ ተገኘ::

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ግን "ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ የተረገመ ይሁን። ገላ ፩፥፰ በማለት አውግዟቸዋል::


ለማንኛውም ያላችሁን አስተያየት new2zewdu16@gmail.com ብላችሁ ኢሜይል ብታደርጉልኝ ደስ ይለኛል::

በዘመነ ዮሐንስ ስለ ልደተ ክርስቶስ የተሰጠው መግለጫ

ልደተ ክርስቶስ - በዘመነ ዮሐንስ (ሙሉውን ጋዜጣ ማንበብ ይችላሉ)

መድሎተ አሚን መጽሐፍ

መድሎተ አሚን (መጽሐፉን ማንበብ ይችላሉ)

ክርስቶስ - መሲህ - ማስያስ - ቅቡዕ - የተቀባ ዮሐ ፩፥፵፩

Friday, September 21, 2018

ጥያቄ ቁ ፫:- ወልድ ቅብዕ፣ በተዋህዶ ከበረ ብላችሁ ለምታምኑ በሙሉ:-


1. “አብ ቀባዒ ወልድ ተቀባዒ መንፈስ ቅዱስ ቅብዕ” ብለው ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን አስተምረው እናንተ ለምን የለም/አላስተማሩም አላችሁ?
፠ “እስመ ብሂለ ክርስቶስ ይመርህ ኀበ አብ ቀባዒ ወኀበ ወልድ ተቀባዒ ወኀበ መንፈስ ቅዱስ ቅብዕ (ዮሐ/አፈ_ወርቅ_በድርሳኑ)”
፠ “አብ ቀባዒ ወወልድ ተቀባዒ ወመንፈስ ቅዱስ ቅብዕ” መጽሐፈ ዝክሪ የብራና ገጽ 78/የትርጓሜ ሊቅ/
፠ “እስመ ዝክረ ክርስቶስ ይመርኀ ኀበ ሰለስቱ አካላት ዝውእቱ አብ ቀባዒ ወልድ ተቀባዒ ወመንፈስ ቅዱስ ቅብዕ (ኪርያኮስ እና ቅ/ቄርሎስ በድርሳኑ)::”

ስለ ልደተ ክርስቶስ የተሰጠ መግለጫ - ዘመነ ዮሐንስ

ልደተ ክርስቶስ በዘመነ ዮሐንስ ታህሳስ ፳፱ ቀን ብቻ እንደሚከበር ሲናገር
በዜና ቤተ ክርስቲያን ጋዜጣ 62ኛ ዓመት ቁ.69 ከኅዳር- ታህሳሥ 2008 ዓ/ም 
ልደተ ክርስቶስ ሁልጊዜ/በ4ቱም ዘመን/ ታህሳሥ 29 ቀን ብቻ እንዲከበር የተሰጠ መግለጫ

“ ልደተ ክርስቶስ በዘመነ ዮሐንስ [በሊቀ ማእምራን ብርሃነ መስቀል አጠና ]
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት “እነሆ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራችን እነግራችኋለሁና አትፍሩ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና” ሉቃ 2፥10-11 ተብሎ የተነገረለት ሰዎችና መላእክት በአድነት የዘመሩለት እጅግ ከፍ ያለ ታላቅ የበዓላት ራስ ነው፡፡ ስለሆነም በዓለም ያሉ ክርስቲያኖች ሁሉ በየዓመቱ በፍጹም ደስታ ያከብሩታል፡፡

Thursday, September 20, 2018

ጥያቄ ቁ ፪:- ወልድ ቅብዕ፣ በተዋህዶ ከበረ ብላችሁ ለምታምኑ በሙሉ:-



፩፦ በምስጢረ ቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ነስዓ ተወክፈ አለ የለም?
ከሌለ ነስአ ብሎ የባህሪ የሚል ወመንፈስ ቅዱስ ይነስእእምኔሆሙ በከመ ይቤ እግዚእነ እስመ እምዚአየ ይነስ - መንፈስ ቅዱስ ከአብ ልብነትን ከወልድ ቃልነትን ገንዘብ ያደርጋልና ሲል እርሱ ራሱ ወልድም ቃልነት ከእኔ አድርጓል ተናግራል ሃ.አ ፫:፷ ለምን አለ። 
★ተወክፈ ብሎ የባህሪ እንዲሆን አመ ተወክፍየ አግዚአብሔር አብ መንግስቶ - እግዚአብሔር አብ መንግስቱን እጀ ባደረገ ጊዜ፩ቆሮ.፲፭፥፳፬
ዳግመኛም ዘይትወከፍ ፀሎተ ንፁሐን=የንጹሐንን ፀሎት የሚቀበል መፅ.ኪዳን
★ኃደረ የባህሪ የሚል ዘየኃድር ውስተ ብርሃን ሀበ አልቦ ዘይቀርቦ - የሚቀርበው ብርሃን በሌለ ውስጥ የሚኖር እርሱ ነው። ወዳ.ማ.ዘሰሉ.
ዳገመኛም አም ውስተ ዛቲ ደመና ብርሃን ኢትትረከብ ኃበ የኃድር እግዚአብሔር - ምንምብርሃን በሌለባትደመና እግዚአብሔር  ድርባታል። አረ.መንፈ.ደር፮ ይህ ሁሉ ለምን ተፃፈ።

"እራሳቸው በክህደት ሳሉ ሌላውን ያወግዛሉ - እንዘ ቦ በክህደት ያወግዙ ካልአ " አውሳቢዮስ


ወመኑ ሐሳዊ ዘእንበለ ዘይክህል ወይብል ከመ ኢየሱስ ኢኮነ መሲሕ ፡ ኢየሱስ መሲሕ (የተቀባ) አይደለም ብሎ ከሚክድ በቀር ሐሠተኛ ማነው? ፩ዮሐ ፫፥፳፪   "መኑ ውእቱ ክርስቶስ - ክርስቶስ ማነው? "


✿አንብብዋ ለመልዕክት እምጥንታ እስከ ተፍፃሜታ ሃ.አዘአንፆኪያ (፻፰፥-፳)✿

በክርስቶስ ሰው መሆን አለምን በክህደት ውስጥ ምንኛ እንደገባ ይገርመኛል። ለመሆኑም ብዙ ሠዎች ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ግንዛቤ ምንኛ ያውቁ ይሆን? እንግዲህ ከስሙ ትርጓሜ ስንነሳ
  ክርስቶስ - በጽርዕ
  መሲሕ -  በአረብ
ቅቡዕ - በግእዝ
                                                  የተቀባ - በአማረኛ ተብሎ ይተረጎማል(ዮሐ ፩፥፵፩ ትርጓሜ)።
ክርስቶስ የሚለውን ስም የመሠከረለት የመጀመሪያ ሊቀ ጳጳስ ሐዋርያው ጴጥሮስ እንደሆነ መጽሐፍ ይመሰክራል።ሉቃ.፱፥፳.......ለብቻው ሲፀልይ ደቀመዛሙርቱ ከርሱ ጋር ነበሩና እኔ ማን እንደሆንሁ ይላሉ ብሎ ጠየቃቸው።............ጴጥሮስም መልሶ "አንተ ውእቱ መሲሑ ለእግዚአብሔር - አንተ ከእግዚአብሔር የተቀባህ ነህ " አለው። አንድም ስለመሠከረለት ጳጳስ ሾሞታል። የመንግስተ ሰማያት መክፈቻ ሠጥቶታል። የተቀባህ ብሎ ቅዱስ ጴጥሮስ መሠከረለት።
አንድም ዘተሰምየ ክርስቶስሃ በእንተዝ ዘተቀብአ ምስሌነ ከመ ሰብእ - በስጋው ስለከበረ(ስለተቀባ) ክርስቶስ ተባለ ቄር.ቃለ ግዘ ፯፥፳፱ ። ወቅብዓቱሰ ዘተወክፈ በትስብእቱ፡መንፈሰ ቅዱስን ተቀበለ መባሉም በስጋው ነውአንድም ከበረ መባሉም በስጋው ነው

Wednesday, September 19, 2018

አባ አስራት ገዳም ዘደብረ ማርቆስ


የአባ አስራተ ማርያም መድኃኒዓለም ገዳም

አባአስራት ገዳም ከደብረ ማርቆስ ከተማ በስተደቡብ ከከተማዋ በግምት 8 ኪሎ ሜትር ላይ ይገኛል፡፡ ከከተማው ወደ አዲስ አባባ በሚወስደው አስፋልት መንገድ በስተቀኝ በኩል ገባ ብሎ ገዳሙ እስከሚገኝበት ስፍራ የ20 ደቂቃ እግር ጉዞ ይወስዳል ፡፡

አባ አስራት ገዳም በ1815 ዓመተ ምህረት አባ አስራት በተባሉ ሰው አማካኝነት የተቆረቆረ እንደሆነ አባቶች ያስረዳሉ፡፡በአመት ሁለት ጊዜ ማለትም በመጋቢት እና ጥቅምት 27 ቀን ከመቼውም በበለጠ ሁኔታ በዓለ ንግሱ የሚከበር ሲሆን ገዳሙ በአሁኑ ሰዓት 57 ወንድና 20 ሴት ያህል መነኮሳት ይኖሩታል ፡፡ በገዳሙ የሴቶች ና የወንዶች ቤተ-ፀበል የተለየ ሲሆን ጫካውን ከሰሜን ወደ ደቡብ ለሁለት የሚከፍለው የጨሞጋ ወንዝ ለገዳሙ ትልቅ ድባብ አጎናፅፎታል፡፡

ከገዳሙ በታች የሚገኘው ደን ውስጥ የተለያዩ የዱር እንስሳት እንደ ጅብ፣ ቦሆር፣ፌቆ ፣ድኩላ፣ ከርከሮ፣ ዝንጀሮ የመሳሰሉት ይገኙበታል ከሀገር በቀል ዛፎች ደግሞ የሀበሻ ፅድ ፣ሰሳ፣ሾላ፣ዋርካ፣ዶግ፣ ጥቁር እንጨት እና ግራር የመሳሰሉት በዉስጡ ይዟል፡፡ ገዳሙ ለእይታ ከሚያምር ገደላማ መልክዓምድራዊ አቀማመጥና ከተፈጥሮ ደን ዉስጥ መገኘቱ ማራኪ እይታ አለው፡፡

ቆጋ ኪዳነ ምህረት አንድነት ገዳም


ቆጋ ኪዳነ ምህረት አንድነት ገዳም
የቆጋ ኪዳነ ምህረት አንድነት ገዳም ከፊል ገጽታ

ከእለታት አንድ ቀን የደረቤ አስተዳዳሪ የነበሩት ምንተግዜር ለአደን ግሜ/ጨሞ/ ወደ ተባለ በርሃ ይሄዳሉ፡፡ በአደን ላይ እያሉ አለምን ንቀው ምነና ላይ ያሉ ክፍለ ኪሮስ የተባሉ አባት ያገኛሉ፡፡ ባህታዊውም ሲሶ እነሴ ውስጥ በምስራቅና በምዕራብ የተከበበች ሸጥ ትገኛለች፡፡ መኖሪያህ ከዚያች ቦታ ይሆናልና ወደዚያች ሂድ፡፡ ቦታዋ በደረስክ ጊዜ እቃ ታገኛለህ፡፡ እቃውን በተገቢው ቦታ አስቀምጠው፡፡ አፅሜንም ወደዚያች ቦታ ወስደህ ያስቀመጥክልኝ እንደሆነ እስከ እለተ ምፃት ድረስ ቦታውን በእረዴት አልለየውም ብለውት ባህታዊው ከምንተግዜር ይሰወራሉ፡፡

ስለ ምስጢረ ተዋህዶና ምስጢረ ቅብዓት፣ ስለ ልደትና ጥምቀት የሚናገር ጽሑፍ

ርቱዓነ ሃይማኖት ዘኢትዮጵያ  (መጽሐፉን ማንበብ ይችላሉ)

ጥያቄ ቁ ፩:- ወልድ ቅብዕ፣ በተዋሕዶ ከበረ ብላችሁ ለምታምኑ በሙሉ:-

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!


1ኛ‹‹‹‹‹‹‹‹“ለሊሁ ቀባዒ ወተቀባዒ ወለሊሁ ቅብዕ…ራሱ አክባሪ ራሱ ከባሪ ራሱ ክብር ነዉ” የሚለዉን ቃል ከሚከተሉት ቃላት ጋር አስማምታችሁ ተርጉሙልን እስኪ?
 [መላሽ ባይኖርም እኛ ጠያቂዎች ግን አለን]

ሀ‹‹‹‹‹‹ “ወበከመ ለአብ ቦቱ ሕይወት ኀቤሁ ለወልድኒ ወሀቦ ሕይወተ ከመ ይኩን ሕይወት ኀቤሁ….. ለአብ ከእርሱ ዘንድ ሕይወት እንዳለው ሕይወት ከእርሱ ይሆን ዘንድ ለወልድም ሰጠው፡፡” (ዮሐ.5፣26-27)፡፡

ለ‹‹‹‹‹‹ “ዘተሠርዐ ወልደ አግዚአብሔር ቅብዐ መንፈስ ቅዱስ…..በመንፈስ ቅዱስ ቅብዐት
የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ ተባለ፡፡” (ተረፈ ቄርሎስ ምቅዋም 8 ገጽ 22)

ሐ‹‹‹‹‹‹‹ “ወለብዕለ ህላዌ መለኮት ንሕነ ንሬእዮ በልዕልና ስብሐቲሁ ዘውእቱ ላዕለ ኵሎሙ ፍጡራን ወአምጣነ ንዴተ ትስብእት ዘነሥአ ይትበሀል ከመ ውእቱ ተሰብሐ እምአብ፤ ወዝንቱ ዓዲ ይትሜሰል ዘተብህለ ከመ ውእቱ ነሥአ ስብሐተ ወመንግስተ  ሥልጠነ ላዕለ ኵሉ ነሢእሰ ይትበሀል በእንተ ዐቅመ ትስብእቱ ወንሕነ ነአምር ከመ ውእቱ እግዚአ ስብሐት በመለኮቱ ወይነብር ምስለ አብ ወአልቦቱ ሕጸጽ በምንትኒ እምልዕልና ስብሐተ ወላዲሁ ወኢእምነ ግብሩ ዘስንዕው በህላዌ መለኮቱ ዝ ወእተ አምሳል ወበተአምኖቱ ንከውን ዕሩያነ…….
የባሕርየ መለኮትን ክብር ከፍጡራን ሁሉ በራቀ በልዑል ጌትነቱ እንዳለ እኛ እናውቀዋለን፤ የተዋሐደው ሥጋ ክብርን የሚሻ በመሆኑ መጠን ከአብ ክብርን ገንዘብ አደገ ይባላል፤ ይህም ጌትነትን መንግሥትን በሁሉ ላይ ሥልጣንን እርሱ ገንዘብ እንዳደረገ የተነገረውን ይመስላል፤ ክብርን ገንዘብ አደረገ መባሉ ሰው ስለመሆኑ ይነገራል፤ በመለኮቱ የክብር ባለቤት እንደሆነ፤ ከአብ ጋርም እኩል ትክክል እንደሆነ ከአባቱ ልዑል ጌትነት፤ በባሕርየ መለኮቱም አንድ ከሚሆንበት ግብሩ በምንም በምን ሕጸጽ እንደሌለበት እናውቃለን፤ አምነን አንድ የምንሆንበት ትምህርት ይህ ነው፡፡ (ዳን. 7፣ 13-255፤ ዮሐ. 12፣18፤17፣1፣-6)፣ (ሃአ ም. 79፣75)

Tuesday, September 18, 2018

“እንጠያየቅ ክፍል 1”


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ!
ይድረስ፦ ለሰሚ ጆሮና ለአስተዋይ እዝነ ልቡና ሁሉ!
============================


ራሳችሁን “ተዋሕዶዎች” እያላችሁ የምትጠሩና ፣ በተለምዶና በአለአዋቂዉ ማንነታችሁ “ቅብዐቶች” እያላችሁ የምትጠሩን ነገር ግን መሢሐዉያን ፣ ቅቡዓን ፣ ክርስሳዉያን ፣ ኦርቶዶክሳዉያን የምንባል እኛን በቤታችሁ “ተዋሕዶ” የሚለዉን የምሥጢረ ሥጋዌ ዘዉግ የማናምን የሚመስላችሁ ለምንድን ነዉ? ብዙዎቻችሁ የቅብዓቱን ምሥጢርና ጣዕመ ትርጓሜ ባታዉቁት “ቅብዐቶች” እያላችሁ ስትጠሩን ይህንን መጥሪያ ሰም ከየት አገኛችሁልን? ማለትም ከመጽሐፍ ወይስ ከመምሕር? መቼም ካላበዳችሁ በስተቀር ከመጽሐፍም ከመምሕርም አገኘነዉ አትሉንም ፡፡ ምክንያቱም መጽሐፍ “አንትሙሰ ቅብዐት ብክሙ እምነ መንፈስ ቅዱስ” ብሎ ተናገረ እጅን “አንትሙሰ ቅብዐት” ብሎ አልተናገረምና ፡፡ ታዲያ ከየት አመጣችሁት?

እንዲሁም መጻሕፍትና ሊቃዉንት ተባብረዉ “ንሕነሰ ኦርቶዶክሳዉያን ፣ ንሕነሰ መሢሐዉያን ፣ ንሕነሰ ክርስቶሳዉያን” ብለዉ ተናገሩ እንጅ “ንሕነሰ ቅብዐት” አዉ “ንሕነሰ ተዋሕዶ” አላሉም ፡፡ ብለዋል የሚል ካለ መረጃዉን ይዞ ከች ይበልና አብረን እንተራረምበት ፡፡ እኔ ለተከታታይ 7 ዓመታት እንዳጠናሁት ግን “ተዋሕዶዎች” እያላችሁ ራሳችሁን የምትጠሩ ወንድሞች እህቶች ፣ እናቶች አባቶች ፣ መምሕራንና ሊቃዉንት “አነ ዉእቱ ፈጣሆሙ ለእሉ ፍጡራን “ እንዳለዉ እደ ዲያብሎስ ሳታዉቁት ራሳችሁን “እኛ ክርስቶሶች ነን” እያላችሁ እደሆነ አለማወቃችሁን ነዉ ፡፡ በተለይ በተለይ ይህ የግቢ ጉባዔ አዳራሽ በሦስት ወርም ፣ በ3 ደቂቃም መምህር እያለ የሚሰይማችሁማ! መቼም ሊቀ ሊቃዉንት የሆን ሁሉ ነዉ የሚመስላችሁ ፡፡ 

Monday, September 10, 2018

ንዋየ ቅድሳቱ በንብ እና በነብር የሚጠበቅባት


ደብረ ወርቅ ማርያም ገዳም (በ ፫፻፶፩ ዓ/ም ተመሰረተች)

በደጉ ዮሐንስ የተሰራው ዕቃ ቤት
ደብረ ወርቅ ማርያም ገዳም [በ፫፻፶፩ ዓ.ም ተመሰረተች]


የአብነት ትምህርት ቤት መማርያ ጎጆዎች


ደብረ ወርቅ ማርያም ገዳም በምስራቅ ጎጃም ዞን በእናርጅ እናዉጋ ወረዳ በወረዳዉ ዋና ከተማ ደብረወርቅ ለእይታ በሚማርክ ቦታ ላይ ትገኛለች፡፡ ቀደም ሲል "ምስካበ ቅዱሳን" የምትባለዉ ገዳሟ በ351 ዓ/ም እንደተመሰረተች ይነገራል፡፡በኋላም በዮዲት ጉዲት ተቃጥላለች፡፡በ1372 ዓ/ም በቀዳማዊ አጼ ዳዊት እንደገና ታንጻ በድጋሜ በ1553 በአጼ ገላዉድዮስ በኖራ ወብ ሆና ታድሳለች፡፡ 

Sunday, September 9, 2018

ክርስቶስ ማለት የስሙ ትርጓሜ




የሕያዉ አምላክ ወልደ እግዚአብሔር ሕያዉ ወልደ ማርያም ሥግዉ ኢየሱስ ክርስቶስ የተቀብዖ ስሙ ከመጽሐፈ ሰዋሰዉ ወግስ መዝገበ ቃላት ሐዲስ ገጽ549-550 ላይ ያለዉ ትርጉም ቃል በቃል እንዲህ ይለናል፡፡

ወልድ ቅብዕ የማንልበት ምክንያት

                                                በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!





የሕያዉ አምላክ ወልደ እግዚአብሔር ሕያዉ ወልደ ማርያም ሥግዉ ኢየሱስ ክርስቶስ የተቀብዖ ስሙ ከመጽሐፈ ሰዋሰዉ ወግስ መዝገበ ቃላት ሐዲስ ገጽ549-550 ላይ ያለዉ ትርጉም ቃል በቃል እንዲህ ይለናል፡፡

Saturday, September 8, 2018

ጥንታዊቷ ደብረ ወርቅ ማርያም ገዳም



መስዋዕተ ኦሪት ሲሰዋባት የነበረችው ጥንታዊቷ ደብረ ወርቅ ማርያም ገዳም




                      የታላቋና የጥንታዊቷ ደብረ ወርቅ ማርያም ገዳም  ዘጋቢ ፊልም

ገድለ እስትንፋሰ ክርስቶስ [ ረከብናሁ ለማስያስ - በዲ/ን ትንሣኤ ደምሴ ]


ዘበትርጓሜሁ ይብልዎ ክርስቶስ (ዮሐ. ፩ ፥፵፪)
በትርጓሜው ክርስቶስ የሚሉት ማስያስን አገኘነው!!!
ይድረስ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት በሙሉ

ምዕራፍ ፬
የጻድቁ የአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ሃይማኖት

※※※※※※※※※※† † † † ※※※※※※※※※※

በዚህ ምዕራፍ የምናየው ጻድቁ ከፈጣሪያቸው ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ስለሃይማኖት ያደረጉትን ንግግርና የልመና ቃል የብራናውን ገድላቸውን ከሕትሙ ገድላቸው ጋር እያነፃጸርን የምናይ ይሆናል፡፡
ሰው ከሌሎቹ ፍጡራን ኹሉ ልዩ የተለየ የሚያስብለው አንዱ ነገር በጎውንም ይኹን ክፉውን ነገር በሕሊናው አሰላስሎ በአእምሮው አመዛዝኖ፣ የተረዳውን ያህል እና የወደደውን ነገር የሀሳቡ መሰብሰቢያ አዳራሽ ወደኾነው ወደቅንጭላቱ ክፍል ማስተጋባቱ ነው፡፡ በመኾኑም ወዳጆቼ ይህን የጻፍኩትን መልእክት /ጽሑፍ/ አቡነ አስትንፋሰ ክርስቶስ የሚያምኑበትን ሃይማኖት ሲኾን ጽሑፉም የተወሰደው፤
1ኛ . . ከብራናው የገድላቸው መጽሐፍ (ሰሜን ወሎ ክፍለ ሐገር ዳውንት ከተባለች ገዳም የተገኘ)
2ኛ . . ከሕትሙ የገድላቸው መጽሐፍ (በአሁኑ ሰዓት በገበያ ላይ የሚገኝ) ገጽ ፲፱-፳፩ ነውና ለማንበብ ቅን ልቦና ያላችሁ ኹሉ በተለይ ግዕዝ ልሳን የምታውቁ ምሁራን ወንድሞቼ እና አባቶቼ የብራናውን ከሕትሙ እያነጻጸራችሁ እንድታዩት በትህትና አደራ እላለሁ፡፡ ንጽጽሩንም ካያችሁ በኋላ ሰው እንደመኾናችሁ መጠን ራሳችሁን ዳኛ አድርጋችሁ የፈረዳችሁትን ውሳኔ ለሌሎች ብታካፍሉ መልካም ነገር ይኾናል ብየ አምናለሁ፡፡

Friday, September 7, 2018

ምስጢረ ቅብዓት በቅዱሳት መጽሐፍት

ስለ ምስጢረ ቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ የተነገረበትን ከቅዱሳት መጽሐፍት እስኪ እንመልከት


ቄርሎስ በሐይማኖት አበው ፣ዮሐንስ አፈወርቅ በድርሳኑ፣ ነብያት በትንቢታቸው፣ ኢጲፋንዮስ በስነ- ፍጥረት መጽሐፉ፣ሰማዕታት በገድላቸው፣ዝክሪናጳውሊ በብራና መጽሐፋቸው፣አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ ምስጢር፣ በመጽሐፍ ቅዱስ እና ሌሎችም ስለተቀባ የሚናገሩ መጽሐፍትን ዘርዝረን ባንጨርስም እነርሱ ያቆዩንን ሃይማኖት እንካድ ብንል አይሰድምና ነው፡፡

1. ከመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ ጥቂቶቹን ስናይ
ኢሳ 61÷1 ማቴ 1÷16 (አንድምታ ትርጓሜ ) መዝ 2÷2 ሐዋ 10÷38 ዕብ 1÷8፤ መዝ 44÷7 1ኛ ዮሐ 2÷20 ሮሜ 1÷4 ዳን 9÷25 (24) ማር 8÷29 ዮሐ 5÷26 ሐዋ 4÷25-28 ሉቃ 9፥20 እንዲሁም ሌሎች የመፅሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ይገኛሉ::

2. መጽሐፈ ሚስጢር 20÷40-41 (አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ) "……… ለእግዚአብሔር የተለየ የተቀባ የሆነ የስሙ ትርጉም መሲሕ የሆነ ክርስቶስ እስከ ተወለደ ድረስ በገሊላ ነገሥታት ዘንድ መሲሕ ተብሎ መጠራት አልነበረም ፡፡ ክርስቶስም መሲሕም ናዝራዊም በማለት በአንድነት የተቀባ ተባለ መሲሕ ፡፡ መሲሕ የተቀባ ማለት ነው፡፡ ክርስቶስ የተባለ ኢየሱስ ተወለደ የተቀባ መባል በእርሱ ተፈፀመ፡፡"

ደብረ ወርቅ ማርያም ገዳም




ጥንታዊቷ ደብረ ወርቅ ማርያም ገዳም

ደብረ ወርቅ ማርያም ገዳም በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት በእናርጅና እናውጋ ወረዳ ከአዲስ አበባ 290 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡ የኦሪት መሥዋዕት ሲሰዋባቸው ከቆዩት ቅዱሳት መካናት አንዷ ናት፡፡ በተለይም ከ250-351 ዓ.ም መሥዋዕተ ኦሪት ሲሰዋባት እንደቆየች የጽሑፍ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡