ከብራና ወደ ወረቀት የተቀየሩ የቅዱሳን አበው መጽሐፍት [ስርዋጽም የተጨመረባቸውም ብዙዎች አሉ] |
ቅዱሳን አበውን "የኑሮአቸውን ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነት ምሰሏቸው" ዕብ ፲፫፥፯ ብሎ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንዳስተማረን እኛም እነርሱን አብነት አድርገን ትንቢታቸውን፣ ስብከታቸውን፣ ድርሳናቸው፣ ገድላቸውን ተቀብለን ለዘመናት ኖረናል እየኖርንም እንገኛለን ::
ነገር ግን በቀደሙት ሐዋርያትና በሊቃውንት እግር የተተኩት የዘመናችን መምህራን ቅዱሳን አበው የተናገሩትን ትክክል አይደለም በማለት የራሳቸውን ሀሳብ እየጨመሩ [ስርዋጽ -አዲስ ነገር እያስገቡ]ና የነበረውን ደግሞ እያስወጡ በማር የተለወሰ መርዝ በኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ እየዘሩ ይገኛሉ::
ነገርግን እኛ ይህንን በመረዳት ለምን እንዲህ ታደርጋላችሁ ብለን ብንጠይቅም ምላሽ ስላልተገኘ እያንዳንዷን ጉዳቸውን ከቀደሙት አበው መጽሐፍት እያወጣን እንዴት እንዳወጡትና እንደጨመሩበት በግልጽ ለመወያየት ይህንን ጦማር መፍጠር አስፈላጊ ሆኖ ተገኘ::
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ግን "ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ የተረገመ ይሁን። ገላ ፩፥፰ በማለት አውግዟቸዋል::
ለማንኛውም ያላችሁን አስተያየት new2zewdu16@gmail.com ብላችሁ ኢሜይል ብታደርጉልኝ ደስ ይለኛል::
በጣም ደስ ይላል በርቱልን እግዚአብሔር አምላክ ያበርታቹህ እውቀትና ጥበብ ይጨምርላቹህ ትዕግስትና ማስተዋሉንም እንዲሁ ያብዛላችህ!!! ❤
ReplyDelete