Monday, December 31, 2018

ዘመንና ትርጉም (መዝ 44፥7)


"በመካከላችሁ ደግሞ ሐሰተኞች አስተማሪዎች ይሆናሉ፤ እነርሱም የዋጃቸውን ጌታ እንኳ ክደው የሚፈጥንን ጥፋት በራሳቸው ላይ እየሳቡ የሚያጠፋ ኑፋቄን አሾልከው ያገባሉ" ፪ኛ ጴጥ ፪-፩ ብሎ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ እንደተናገረው የዘመኑ ሊቃውንትና የቀድሞ ሊቃውንት ትርጓሜ ልዩነት እንደልቤ በተባለው የእስራኤል ንጉስ ቅዱስ ዳዊት “በእንተዝ ቀብዐከ እግዚአብሔር አምላክከ ቅብዓ ትፍሥሕት እምእለ ከማከ -- ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክህ እንዳንተ ካሉት ይልቅ የደስታ ዘይትን ቀባህ” መዝ 44፥7....... ብሎ የተናገረው እኮ እግዚአብሔር ወልድ በኋለኛው ዘመን ሥጋ አዳምን ሲለብስ የአብ፣ የወልድ፣ የመንፈስ ቅዱስን ግብር በግልጽ መናገሩ እንጅ የሦስቱንም ግብር ጠቅልሎ ለወልድ[ቃል] ብቻ መስጠቱ አይደለምና ልብ ልንል ይገባናል::
......በተዋሕዶ ከበረ ባዮች[ካሮች] “ቀብዓከ እግዚአብሔር አምላክከ -- እግዚአብሔርነትህ አምላክነትህ አከበረህ” ብለው እራሱ አክባሪና ክብር ሥጋ ደግሞ ከባሪ ነው ለሚለው ምንፍቅናቸው መሸፈኛ ይሆን ዘንድ ትርጓሜን እያጣመሙ ይገኛሉ::

Thursday, December 27, 2018

ከወደ ፡ ወልድያ ፡ የመጣችው ፡ የካሮቹ ፡ የምፍቅና ፡ ጥያቄ ፡       እና ፡ ኦርቶዶክሳዊ ፡ መልሷ ፡፡

ከወደ ፡ ወልድያ ፡ የመጣችው ፡ የካሮቹ ፡ የምፍቅና ፡ ጥያቄ ፡       እና ፡ ኦርቶዶክሳዊ ፡ መልሷ ፡፡
===================================================
የተከበራችሁ ፡ ኦርቶዶክሳውያን ፡ ሁላችሁም ፡ በማስተዋል ፡ ተከታተሉኝ ፤ ይህች ፡ የካሮቹ ፡ የጨዋ ፡ ጥያቄአቸው ፡ ምንጫ ፡ የምዕራባዊት ፡ ጎጃም ፡ የሊቃውንት ፡ ጉባዔ ፡ ሰብሳቢና ፡ የዐራቱ ፡ ጉባዔ ፡ መምህር ፡ የሚባሉት ፡ የስምዐኮነ ፡ መልአክ ፡ ቃለ ፡ ጽድቁ ፡ ለአብ ፡ የተሰኘች ፡ መጽሐፍ ፡ ናት ፡፡ እኒህ ፡ ሳያላምጡ ፡ የሚውጡ ፡ አግበስብሶች ፡ መጽሐፏን ፡ ሳይመረምሩ ፡ እንዳለች ፡ውጠው ፡ እያነቀች ፡ ገደል ፡ እየለቀቀቻቸው ፡ ይገኛሉ ፡፡ እነሆም ፡ ይሕች ፡ ክሕደት ፡ ከምዕራብ ፡ ጎጃም ፡ ተነስታ ፡ ስሜን ፡ ወሎ ፡ ወልድያ ፡ ደርሳ ፡ ነጥራ ፡ ወደሸዋ ፡ ተመልሳለችና ፡ ክሕደቷን ፡ እንዳለች ፡ አስቀምጥ ፡ እና ፡ በብልት ፡ በብልቷ ፡ ክሽን ፡ ባለች ፡ የኦርቶዶክሳውያን ፡ ልሳን ፡ ለማበጠር ፡ አሐዱ ፡ ብያለሁ፡፡ ሙሉ ፡ ጥያቄው ፡ በቴሌ ፡ ግራም ፡ የደረሰኝ ፡ ሲሆን ፡ እንደሚከተለው ፡ እንደወረደ ፡ አቀርበዋለሁ፡፡ ሰውየው ፡ ሲልክልኝ ፡ “ህይወት” ፡ ያለውን ፡ “ሕይወት” ፡ “ህድረት” ፡ ያለውን ፡ “ኅድረት” ፡ ከማለት ፡ በስተቀር ፡ አልጨመርኩም ፡ አልቀነስኩም ፡፡
ሙሉ ፡ ጥያቄው‹‹‹‹‹‹‹‹‹ “ቃል ፡ ለተዋሐደው ፡ ሥጋ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ሕይወት ፡ ሆነው ፡ ሲባል ፤ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ አካላዊ ፡ እስትንፋስ ፡ መሆኑ ፡ እርግጥ ፡ ነው ፤ ታዲያ ፡ ለሥጋ ፡ ሕይወት ፡ የሆነው ፡ በአካሉ ፡ ነው ፡ ወይስ ፡ በፀጋው? በፀጋው ፡ ነው ፡ ከተባለ ፡ ቃል ፡ ሥጋ ፡ ሆነ ፡ ብለናልና ፡ በቃልና ፡ በሥጋ ፡ መካከል ፡ ልዩነት ፡ ወይም ፡ ሁለትነት ፡ የለምና ፡ የቃል ፡ ሕይወት ፡ የጸጋ ፡ ሕይወት ፡ መሆኑ ፡ ነው ፡፡ የጸጋ ፡ ሕይወት ፡ ያለው ፡ አምላክ ፡ ደግሞ ፡ የለንም ፡፡ እንዲህ ፡ ከሆነ ፡ እርሱ ፡ ፍጡር ፡ አምላክነቱም ፡ የጸጋ ፡ መሆኑ ፡ ስለሆነ ፡ እንዲህ ፡ ማለትንም ፡ አምላክ ፡ ከእኛ ፡ ያርቅልን ፡፡ እንዲሁም ፡ ሕይወት ፡ የሆነው ፡ በአካሉ ፡ ነው ፡ ከተባለ ፤ ደግሞ ፡ ሌላ ፡ ጥያቄ ፡ ያስነሳል ፡፡ ይኸውም ፡ ሥጋ ፡ የመንፈስ ፡ ቅዱስን ፡ ሕይወትነት ፡ የተቀበለው ፡ በተዋሕዶ ፡ ነው ፡ በኅድረት?በኅድረት ፡ እንዳይባል ፡ ቃል ፡ ሥጋ ፡ ሆነ ፡ ስላልን ፡ ምንታዌ ፡ ስለሌለ ፡ አንዱን ፡ አካል ፡ በአንዱ ፡ ማሳደር ፡ ይሆንብናል ፤ በሥላሴ ፡ ደግሞ ፡ ኃዳሪና ፡ ማኅደር ፡ የለም ፡ በተዋሕዶ ፡ ነው ፡ እንዳንል ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ሰው ፡ ሆነ ፡ ያሰኛል ፤ ቃልንም ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስንም ፡ ከሥጋ ፡ አዋሕዶ ፡ ሁለቱን ፡ አካላት ፡ አንድ ፡ ወደማድረግ ፡ ይወስዳል ፡፡ ስለዚህ ፡ ልንጠነቀቅና ፡ ልንፈራ ፡ የምንናገረውን ፡ ልናስተውል ፡ ይገባናል ፡፡ መንፈስ ፡ ቅዱስን ፡ ተቀባ ፡ (ሕይወት ፡ ሆነው) ፡ ሲባል ፡ በኅድረትም ፡ በተዋሕዶም ፡ ካልሆነ ፡ እንዴት ፡ ሊሆን ፡ ይችላል?”›››››››››››› የሚል ፡ ጥያቄ ፡ ነው
እንግዲህ ፡ ይህንን ፡ ጥያቄ ፡ በብልት ፡ በብልቱ ፡ ለመመልከት ፡ ይረዳን ፡ ዘንድ ፡ ቁጥር ፡ እየሰጠሁ ፡ ከሙሉ ፡ ማሥረጃ ፡ ጋር ፡ አብራራዋለሁ
1ኛ‹‹‹‹‹‹‹‹ “ቃል ፡ ለተዋሐደው ፡ ሥጋ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ሕይወት ፡ ሆነው ፡ ሲባል ፤ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ አካላዊ ፡ እስትንፋስ ፡ መሆኑ ፡ እርግጥ ፡ ነው ፤ ታዲያ ፡ ለሥጋ ፡ ሕይወት ፡ የሆነው ፡ በአካሉ ፡ ነው ፡ ወይስ ፡ በፀጋው?”›››››››ብለሃል ፡ በመጀመሪያ ፡ ደረጃ ፡ ጥያቄው ፡ መሆን ፡ የነበረበት ፡ “በአካል ፡ ነው ፡ በፀጋ” ፡ ሳይሆን ፡ “በባሕርይ ፡ ነው ፡ በፀጋ” ፡ ተብሎ ፡ ነበር ፡፡ ይሁን ፡ እንጅ ፡ ካሮቹ ፡ ሁለመናችሁ ፡ ያልተገራ ፡ ያልተገዘረ ፡  በመሆኑ ፡ የምትጠይቁትን ፡ እንኳን ፡ አታውቁም ፡፡ ሆኖም ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ለወልድ ፡ በትስብእቱ ፡ ክብር ፡ ሆነው ፡ ሲባል ፤ በአካላዊ ፡ የባሕርይ ፡ ኅድረት ፡ እንደሆነ ፡ የአንጾኪያው ፡ ሊቀጳጳስ ፡ ቅዱስ ፡ ሳዊሮስ ፡ እንዲህ ፡ ሲል ፡ ተናግሯል ፤ “ወበእንተዝ ፡ ኵሉ ፡ ይትበሀል ፡ ከመ ፡ ውእቱ ፡ ነሥአ ፡ መንፈሰ ፡ ዚኣሁ ፡ ዘተነግረ ፡ በኢሳይያስ ፡ ነቢይ (ሰው ፡ ስለሆነ ፡ በኢሳይያስ ፡ እንዲህ ፡ ተብሎ ፡ የተነገረ ፡ የባሕርይ ፡ ሕይወቱ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስን ፡ ገንዘብ ፡ እንዳደረገ ፡ ይነገራል) ፤ እንዘ ፡ ይብል ፡ መንፈሰ ፡ እግዚአብሔር ፡ ዘላዕሌየ ፡ በእንተ ፡ ዝንቱ ፡ ቀብዓኒ (የእግዚአብሔር ፡ ሕይወቱ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ በእኔ ፡ ላይ ፡ አለ ፤ ሰው ፡ ስለሆንኩ ፡ ተሰጠኝ ፤ አከበረኝም ፤ ብሎ ፡ በኢሳይያስ ፡ የተነገረ ፡ ሕይወቱ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስን ፡ ገንዘብ ፡ እንዳደረገ ፡ ሊነገር ፡ ይገባል) ፤ ሰበከ ፡ በእንተ ፡ ዝንቱ ፡ እንዘ ፡ ይብል ፡ እስመ ፡ መንፈስ ፡ ዘዚኣየ ፡ በህላዌ ፡ ለሊሁ ፡ ኀደረ ፡ ላዕሌየ (ሰው ፡ ስለሆንኩ ፡ በህልውናዬ ፡ ያለመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ተሰጠኝ ፡ ብሎ ፡ አስተማረ) ፤ ወለምንትኑ ፡ ተሰመይኩ ፡ መሲሐ (እንኪያ ፡ ስለምን ፡ መሲሕ ፡ ተባልኩ) ፤ ዘእንበለ ፡ ዳዕሙ ፡ ሶበ ፡ ኮንኩ ፡ ሰብአ (ነፍስን ፡ ሥጋን ፡ ብዋሐድ ፡ ነው ፡ እንጂ ፡ ብሎ ፡ አስተማረ) ፤ ወዘሰ ፡ ኀደረ ፡ ላዕሌሁ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ በእንተ ፡ ሥርዓተ ፡ ትስብእት ፡ ውእቱ (መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ተሰጠው ፡ የተባለ ፡ ለሰውነቱ ፡ በሚገባ ፡ ነው ፡፡ አንድም ፡ ሰው ፡ ስለሆነ ፡ ስለከበረ ፡ ሥጋ ፡ ነው) ፤ ወእመ ፡ አኮሰ ፡ እስመ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ዘዚኣሁ ፡ ውእቱ ፡ በህላዌ ፡ መለኮት (ሰው ፡ ካልሆነማ ፡ በባሕርየ ፡ መለኮቱ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ገንዘቡ ፡ ነውና ፤ አንድም ፡ የባሕርይ ፡ ሕይወቱ ፡ ነውና ፡ እንደምንተሰጠው ፡ ይባላል) ፤ ዘከመ ፡ እግዚአብሔር ፡ በእግዚአብሔር ፡ በከመ ፡ ይቤ ፡ አብ ፡ ወወልድ ፡ ወመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ፍጹም (አብ ፡ በወልድ ፡ በመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ህልው ፡ ሁኖ ፡ እንዲኖር ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስም ፡ በባሕርየ ፡ መለኮቱ ፡ ገንዘቡ ፡ ነውና ፡ ሰውማ ፡ ካልሆነ ፡ እንደምን ፡ ተሰጠው ፡ ይባላል) ፤ ወዝግብር ፡ ኢኮነ ፡ ክፉለ ፡ ዘከመ ፡ ፩ዱ ፡ እምነቢያት (ይህ ፡ ክብር ፡ ከነቢያት ፡ እንደአንዱ ፡ ሊያከብረው ፤ በተከፍሎም ፡ የተሰጠው ፡ አይደለም) ፤ ወኢበእንተዝ ፡ ኀደረ ፡ ላዕሌሁ ፡ መንፈሰ ፡ እግዚአብሔር ፡ በእንተ ፡ ሥርዓት (በጸጋም ፡ ሊያከብረው ፡ በተከፍሎ ፡ የተሰጠው ፡ አይደለም) ፤ አላ ፡ በከመ ፡ ይቤ ፡ ኢሳይያስ ፡ ነቢይ ፡ ሶበ ፡ ፈቀደ ፡  ይምሀረነ ፡ ፍጻሜ ፡ ግብሩ ፡ ኈለቈ ፡ ዘንተ ፡ 7ተ ፡ ጊዚያተ ፡ ወይቤ ፡ ኀደረ ፡ ላዕሌሁ ፡ መንፈሰ ፡ እግዚአብሔር ፡ መንፈሰ ፡ ጥበብ ፣ መንፈሰ ፡  አእምሮ ፣ መንፈሰ ፡ ምክር ፣ መንፈሰ ፡ ልቡና ፣ መንፈሰ ፡ ኃይል ፣ መንፈሰ ፡ ፈሪሃ ፡ እግዚአብሔር (ለምዕመናን ፡ የሚሰጠውን ፡ ፍጹም ፡ ክብሩን ፡ ያስረዳ ፡ ዘንድ ፡ በወደደ ፡ ጊዜ ፡ ኢሳይያስ ፡ እንዲህ ፡ ብሎ ፡ መላልሶ ፡ እንደተናገረ ፡ ገንዘቡ ፡ ነው ፡ እንጂ ፡ በጸጋ ፡ ሊያከብረው ፡ የተሰጠ ፡ አይደለም ፡፡ አንድም ፡ ለምዕመናን ፡ የሚሰጠውን ፡ ፍጹም ፡ ክብሩን ፡ ያስረዳ ፡ ዘንድ ፡ ኈለቈ ፡ ዘንተ ፡ 7ተ ፡ ጊዜያተ (ይህን ፡ ሰባት ፡ ጊዜ ፡ መላልሶ ፡ ተናገረ ፡ እንጂ) ፤ እስመ ፡ ኍልቈ ፡ ፯ ፡ በኀበ ፡ ዕብራውያን ፡ ፍጹም ፡ ውእቱ (፯ ፡ ማለት ፡ በዕብራውያን ፡ ዘንድ ፡ ፍጹም ፡ ነውና ፡ ለምዕመናን ፡ የሚሰጠውን ፡ ፍጹም ፡ ክብሩን ፡ ያስረዳ ፡ ዘንድ ፡ በወደደ ፡ ጊዜ ፡ ኢሳይያስ ፡ እንደተናገረ ፡ ገንዘቡ ፡ ነው ፡ እንጂ ፡ በጸጋ ፡ ሊያከብረው ፡ የተሰጠው ፡ አይደለም)” ፡ በማለት ፡ ቁልጭ ፡ አድርጎ ፡ ያስረዳል ፡፡ (ሃይ. አበው ፡ ዘሳዊሮስ ፡87 ፡ 17-19 ፡ አንድምታ ፡ በሊቀ ፡ ሊቃውንት ፡ ዕዝራ ፡ የተዘጋጀ) ፡፡ ቄርሎስም ፡ በድርሳኑ ፡ በአካል ፡ ተቀብሎታል ፡ የሚለውን ፡ አጽንቶታልና ፡ ይመልከቱት ፡፡
2ኛ‹‹‹‹‹“በፀጋው ፡ ነው ፡ ከተባለ ፡ ቃል ፡ ሥጋ ፡ ሆነ ፡ ብለናልና ፡ በቃልና ፡ በሥጋ ፡ መካከል ፡ ልዩነት ፡ ወይም ፡ ሁለትነት ፡ የለምና ፡ የቃል ፡ ሕይወት ፡ የጸጋ ፡ ሕይወት ፡ መሆኑ ፡ ነው ፡፡ የጸጋ ፡ ሕይወት ፡ ያለው ፡ አምላክ ፡ ደግሞ ፡ የለንም ፡፡ እንዲህ ፡ ከሆነ ፡ እርሱ ፡ ፍጡር ፡ አምላክነቱም ፡ የጸጋ ፡ መሆኑ ፡ ስለሆነ ፡ እንዲህ ፡ ማለትንም ፡ አምላክ ፡ ከእኛ ፡ ያርቅልን”››››››››ብለህ ፡ ለጠየቅኸው ፡ ቃል ፡ ከላይ ፡ ቅዱስ ፡ ሳዊሮስ ፡ “ወዝግብር ፡ ኢኮነ ፡ ክፉለ ፡ ዘከመ ፡ ፩ዱ ፡ እምነቢያት (ይህ ፡ ክብር ፡ ከነቢያት ፡ እንደአንዱ ፡ ሊያከብረው ፤ በተከፍሎም ፡ የተሰጠው ፡ አይደለም) ፤ ወኢበእንተዝ ፡ ኀደረ ፡ ላዕሌሁ ፡ መንፈሰ ፡ እግዚአብሔር ፡ በእንተ ፡ ሥርዓት (በጸጋም ፡ ሊያከብረው ፡ በተከፍሎ ፡ የተሰጠው ፡ አይደለም) ፤ አላ ፡ በከመ ፡ ይቤ ፡ ኢሳይያስ ፡ ነቢይ ፡ ሶበ ፡ ፈቀደ ፡  ይምሀረነ ፡ ፍጻሜ ፡ ግብሩ ፡ ኈለቈ ፡ ዘንተ ፡ 7ተ ፡ ጊዚያተ ፡ ወይቤ ፡ ኀደረ ፡ ላዕሌሁ ፡ መንፈሰ ፡ እግዚአብሔር ፡ መንፈሰ ፡ ጥበብ ፣ መንፈሰ ፡  አእምሮ ፣ መንፈሰ ፡ ምክር ፣ መንፈሰ ፡ ልቡና ፣ መንፈሰ ፡ ኃይል ፣ መንፈሰ ፡ ፈሪሃ ፡ እግዚአብሔር (ለምዕመናን ፡ የሚሰጠውን ፡ ፍጹም ፡ ክብሩን ፡ ያስረዳ ፡ ዘንድ ፡ በወደደ ፡ ጊዜ ፡ ኢሳይያስ ፡ እንዲህ ፡ ብሎ ፡ መላልሶ ፡ እንደተናገረ ፡ ገንዘቡ ፡ ነው ፡ እንጂ ፡ በጸጋ ፡ ሊያከብረው ፡ የተሰጠ ፡ አይደለም”›››››በማለት ፡ አሥረግጦ ፡ ስለተናገረ ፡ በጸጋ ፡ አላልነውም ፡ ያልተጻፈ ፡ አታንብቡ፡፡
3ኛ‹‹‹‹‹‹ “እንዲሁም ፡ ሕይወት ፡ የሆነው ፡ በአካሉ ፡ ነው ፡ ከተባለ ፤ ደግሞ ፡ ሌላ ፡ ጥያቄ ፡ ያስነሳል ፡፡ ይኸውም ፡ ሥጋ ፡ የመንፈስ ፡ ቅዱስን ፡ ሕይወትነት ፡ የተቀበለው ፡ በተዋሕዶ ፡ ነው ፡ በኅድረት?በኅድረት ፡ እንዳይባል ፡ ቃል ፡ ሥጋ ፡ ሆነ ፡ ስላልን ፡ ምንታዌ ፡ ስለሌለ ፡ አንዱን ፡ አካል ፡ በአንዱ ፡ ማሳደር ፡ ይሆንብናል ፤ በሥላሴ ፡ ደግሞ ፡ ኃዳሪና ፡ ማኅደር ፡ የለም ፤”›››››››ብለህ ፡ ተናግረሀል ፡፡ መንፈስ ፡ ቅዱስን ፡ በአካል ፡ ገንዘቡ ፡ አደረገ ፡ ሥንል ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ሥጋ ፡ ለበሰ ፡ ተዋሐደ ፡ ማለታችን ፡ እዳልሆነ ፡ በደንብ ፡ አድርገህ ፡ ልትረዳው ፡ ተገቢ ፡ ነውና ፡ ከላይ ፡ ሳዊሮስ ፡ እንደገለጠው ፡ “መንፈስ ፡ ዘዚአየ ፡ በህላዌ ፡ ለሊሁ ፡ ኃደረ ፡ ላዕሌየ (የባሕርይ ፡ ሕይወቴ ፡ የሚሆን ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ በኔ ፡ ላይ ፡ አደረ/ተሰጠኝ” ፡ አለን ፡ እንጅ ፤ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ እኔን ፡ ተዋሐደ ፡ አላለም ፡፡ ይህ ፡ ማለት ፡ አካላዊ ፡ የባሕርይ ፡ ኅድረት ፡ ነው ፡ እንደ ፡ ምዕመናን ፡ የጸጋ ፡ አይደለም ፡፡ መንፈስ ፡ ቅዱስን ፡ የተቀበለው ፡ በባሕርይ ፡ ኅድረት ፡ ነውና ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ሥጋን ፡ ተዋሐደ ፡ ወደሚል ፡ ክሕደት ፡ የሚያስገባ ፡ አይደለም ፡ ልንልዎት ፡ እንወዳለን ፡፡ ለዚህም ፡ ነው ፡ ቅዱስ ፡ ሳዊሮስ ፡ “ወበዝ ፡ ግብር ፡ ኢኮነ ፡ ክፉለ ፡ ዘከመ ፡ ፩ዱ ፡ እምነቢያት (ይህ ፡ ክብር ፡ ከነቢያት ፡ እንደ ፡ አንዱ ፡ ሊያከብረው ፡ በተከፍሎ ፡ የተሰጠው ፡ አይደለም)” ፡ ብሎ ፡ ሐተታውን ፡ ልቡናን ፡ ደስ ፡ በሚያሰኝ ፡ ምሥጢር ፡ መናገሩ ፡፡ የምሥጢረ ፡ ቅብዐተ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ፆመኞቹ ፡ መለካውያን ፡ እናንተ ፡ ግን ፤ “ወበዝ ፡ ግብር ፡ ኢኮነ ፡ ክፉለ ፡ ዘከመ ፡ 1ዱ ፡ እምነቢያት” ፡ የሚለውን ፡ ግዕዝ ፡ ስትተረጕሙ ፡ “በዚህ ፡ ግብር ፡ ተዋሕዶ ፡ ጠፍቶ ፡ ከነቢያት ፡ እንደ ፡ አንዱ ፡ የሆነ ፡ አይደለም” ፡ ብላችሁ ፡ ግዕዝንም ፡  ምሥጢረ ፡ መጻሕፍትንም ፡ እንደምትጾሙ ፡ ይህ ፡ ትክክለኛ ፡ ማረጋገጫ ፡ ነው ፡፡
4ኛ‹‹‹‹‹‹‹በተዋሕዶ ፡ ነው ፡ እንዳንል ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ሰው ፡ ሆነ ፡ ያሰኛል ፤ ቃልንም ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስንም ፡ ከሥጋ ፡ አዋሕዶ ፡ ሁለቱን ፡ አካላት ፡ አንድ ፡ ወደማድረግ ፡ ይወስዳል ፡፡ ስለዚህ ፡ ልንጠነቀቅና ፡ ልንፈራ ፡ የምንናገረውን ፡ ልናስተውል ፡ ይገባናል ፡፡ መንፈስ ፡ ቅዱስን ፡ ተቀባ ፡ (ሕይወት ፡ ሆነው) ፡ ሲባል ፡ በኅድረትም ፡ በተዋሕዶም ፡ ካልሆነ ፡ እንዴት ፡ ሊሆን ፡ ይችላል?››››››››››ብለህ ፡ ተይቀሀል ፡ እኛ ፡ የምንለውና ፡ የምናምነው ፡ ወልደ ፡ እግዚአብሔር ፡ ሕያው ፡ ወልደ ፡ ማርያም ፡ ሥግው ፡ በሥግውነቱ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስን ፡ በመላ ፡ በአካል ፡ ተቀብሎ ፡ የባሕርይ ፡ ክብርን ፡ ከበረ ፡ ብለን ፡ እንጅ ፤ በፀጋ ፡ ከበረ ፡ ብለን ፡ አይደለም ፡፡ ተቀበለ ፡ የተባለውም ፡ ስለሥጋ ፡ እንግድነት ፡ ነው ፡፡ በባሕርየ ፡ መለኮቱ ፡ በእርሱ ፡ ህልው ፡ ሆኖ ፡ የሚኖር ፡ የባሕርይ ፡ ሕይወቱ ፡ እንደሆነ ፡ መጻሕፍት ፡ ይመሠክሯል ፡ (ሃይ. አበው ፡ ዘሳዊሮስ ፡ '7 ፡ 07-09) ፡፡ ለጠየቁት ፡ ጥያቄዎት ፡ መልሱ ፡ በፀጋ ፡ ነቢያትን ፣ ሐዋርያትን ፣ ቅዱሳንን ፣ ምዕመናንን ፣ ካህናትን ፡ ያከብረናል ፡፡ የእርሱ ፡ መክበር ፡ ግን ፡ ከእኛ ፡ የተለየ ፡ የባሕርይ ፣ የማይወሰድ ፣ የማይነሣ ፣ ሲሆን ፤ ለሐዋርያት ፣ ለነቢያት ፡ አበው ፣ ለምዕመናን ፡ ለእኛ ፡ ደግሞ ፡ በልክ ፡ በመጠን ፣ በመሥፈርት ፡ የሚሰጥ ፣ የፀጋ ፣ ኃጢአትን ፡ በሠራን ፡ ጊዜ ፡ የሚነሣ ፡ (የሚወሰድብን) ፡ ነው ፡፡ በሐዋርያትና ፡ በክርስቶስ ፡ መካከል ፡ ያለው ፡ ልዩነትም ፡ ሐዋርያት ፡ በፀጋ ፡ ሲከብሩበት ፤ በልክ ፡ መስፈርት ፡ ሲቀበሉት ፤ ክርስቶስ ፡ ግን ፡ የባሕርይ ፡ ክብርን ፡ ከብሮበታል ፤ አልቦ ፡ መሥፈርት ፡ ተቀብሎታል ፤ ልዩነቱ ፡ ይህ ፡ ነው ፡፡  ቅዱስ ፡ ዳዊትም ፡ የእርሱ(የክርስቶስ) ፡ መቀባት(መክበር) ፡ ልዩ ፡ መሆኑን ፡ ሲያጠይቅ ፡ “ቀብዓከ ፡ እግዚአብሔር ፡ አምላክከ ፡ ቅብዓ ፡ ትፍስሕት ፡ እምእለከማከ (እግዚአብሔር ፡ አምላክህ ፡ እንዳንተ ፡ ያሉ ፡ ካህናትና ፡ ነቢያት ፡ ከተቀቡት ፡ ይልቅ ፡ የደስታ ፡ ዘይትን ፡ ቀባህ)” ፡ መዝ ፡ #4 ፡ t ፡ 7) ፡ ብሏል ፡፡ ቅዱስ ፡ ጳውሎስም ፡ ክቡር ፡ ዳዊት ፡ እምእለ ፡ ከማከ ፡ ያለውን ፡ ዘይኄይስ ፡ እምእሊአሆሙ ፡ ብሎ ፡ አጉልቶ ፡ ተናግሯል (ዕብ ፡ ምዕ ፡ 1 ፡ t ፡ 9) ፤ አፈወርቅ ፡ ዮሐንስም ፡ “እስመ ፡ ለእግዚእ ፡ ክርስቶስ ፡ አኮ ፡ በመሥፈርት ፡ ዘተውህቦ ፡ መንፈስ ፡ ይቤ ፡ ቅብዓ ፡ ትፍስሕት ፡ እምእለከማ (መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ለክርስቶስ ፡ በልክ ፡ በመጠን ፡ የተሰጠው ፡ አይደለምና ፡ ቅብዓ ፡ ትፍስሕት ፡ እምእለከማከ ፡ አለ” ፡ ድር ፡ 3 ፡ ብሎ ፡ ዘአልቦ ፡ መሥፈርት ፡ ሲል ፡ ገልጦታል ፡፡ ቅዱስ ፡ ቄርሎስ ፡ ደግሞ ፡ “በቅብዓት ፡ ነከራ ፡ እምእለ ፡ ተሳተፎሙ ፡ ዘውእቶሙ ፡ ንሕነ ( እኛ ፡ ካገኘነው ፡ ክብር ፡ በበለጠ ፡ ክብር ፡ ከበረ ፤ እምእለ ፡ ተሳተፎሙ ፡ የተባልን ፡ እኛ ፡ ነን” ፡ (ጰላድ ፡ 05 ፡ t ፡ 1-9) ፡ በማለት ፡ አወሥጥሮ ፡ ተናግሮታል ፡፡  ቅዱሳን ፡ አባቶቻችን ፡ እንዲህ ፡ እንደነገሩን ፤ የክርስቶስ ፡ መክበር ፡ የባሕርይ ፡ ሲሆን ፤ የሐዋርያት ፡ መክበር ፡ ግን ፡ በጸጋ ፡ ነውና ፡ ልዩነቱ ፡ እንዲህ ፡ ነው ፡፡
ይህ ፡ በእንዲህ ፡ እንዳለ ፡ መገልበጥ ፡ ልማዳችሁ ፡ የሆናችሁ ፡ በተዋሕዶ ፡ ከበረ ፡ ወልድ ፡ ቅብዕ ፡ ብላችሁ ፡ የምታምኑ ፡ ሁላችሁም ፡ ከላይ ፡ እርስዎ ፡ እንደጠቀሱት ፡ “በሦስት ፡ ከፍለን ፡ እንመለከታቸዋለን” ፡ ብለው ፡ የጠቀሷቸውን ፡ በአባ ፡ ጎርጎርዮስ ፡ አባባል ፡ “የቅብዓት ፡ ዘውጎች” ፡ የሚባሉ ፡ ተረት ፡ ተረቶችን ፡ ከኪዳነ ፡ ወልድ ፡ ገልብጣችሁ ፡ አስቀምጣችኋል ፡፡ እስኪ ፡ የሚጠቅም ፡ የሚረባ ፡ ከሆነ ፡ የሰሞንኞቹ ፡ የእናንተ ፡ ባህል ፡ ምን ፡ እንደሚባል ፡ እናስቀምጥላችሁ ፡፡
ጥያቄ ፡ ለዶማው ፡ ቢለዋ
1ኛ‹‹‹‹‹‹በተዋሕዶ ፡ ከበረ ፡ ብለህ ፡ ስታምነው ፡ ማን ፡ ነው ፡ በተዋሕዶ ፡ የከበረው?ማን ፡ አከበረው?ለምን ፡ ከበረ?

Tuesday, December 25, 2018

በስመ ፡ አብ ፡ ወወልድ ፡ ወመንፈስ ፡

ቅዱስ ፡ አሐዱ ፡ አምላክ
ወልደ ፡ አብ ፡ በወልደ ፡ አብ ፡ ክፍል ፡

ዐራት

በቅብዓት ፡ የባሕርይ ፡ ልጅ ፡ ሆነ ፡

ማለት ፡ ምን ፡ ማለት ፡ ነው?
============================================
በቅብዓት ፡ የባሕርይ ፡ ልጅ ፡ ሆነ ፡ ማለት ፡ ምሥጢሩ ፡ ምንድን ፡ ነው? ፡ ቢሉ ፤ ወልድ ፡ በሰውነቱ ፡ የባሕርይ ፡ ሕይወቱን ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስን ፡ በመላ(ካለ ልክ ) ፡ ተቀብሎ ፡ ከአብ ፡ የባሕርይ ፡ ልደትን ፡ ተወለደ ፡ ማለት ፡ ነው ፡፡ ምነው ፡ ይህስ ፡ ቢሆን ፡ በአብ ፡ ያልተወለደ ፣ በራሱ ፡ ያልተወለደ ፣ ስለምን ፡ በመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ተወለደ? ፡ ቢሉ ፤ ይህስ ፡ ወላዲ ፡ በሚመስለው ፡ ሕይወት ፡ ይወልዳል ፡ እንጅ ፡ በማይመስለው ፡ ሕይወት ፡ አይወለድም ፡፡ ለዚህም ፡ ምሣሌ ፡ ያሥረዳል ፤ እንዴት ፡ ያሥረዳል? ፡ ቢሉ ፤ እነሆ ፡ ዛሬ ፡ በደመ ፡ ነፍስ ፡ ሕያዋን ፡ የሆኑ ፡ እንስሳት ፡  ከእንስሳት ፡ ይወለዳ ፤ በነባቢት ፡ ነፍስም ፡ ሕያው ፡ የሆነ ፡ ሰውም ፡ ከሰው ፡ ይወለዳል ፡፡ በደመ ፡ ነፍስ ፡ ሕያው ፡ ያልሆነ ፡ ከእንስሳ ፤ በነባቢት ፡ ነፍስ ፡ ሕያው ፡ ያልሆነ ፡ ከሰው ፡ እንዳይወለድ ፤ እንደዚህም ፡ ሁሉ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ለአብ ፡ ሕይወቱ ፡ ስለሆነ ፡ በመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ሕያው ፡ ያልሆነ ፡ ከአብ ፡ አይወለድምና ፡ በመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ሕይወትነት ፡ ከአብ ፡ ተወለደ ፡፡ “ወበከመ ፡ ለአብ ፡ ቦቱ ፡ ሕይወት ፡ ኀቤሁ ፡ ከማሁ ፡ ለወልድኒ ፡ ወሀቦ ፡ ሕይወተ ፡ ከመ ፡ ይኩን ፡ ሕይወት ፡ ኀቤሁ(ለአብ ፡ በራሱ ፡ ሕይወት ፡ እንዳለው ፡ እንዲሁ ፡ ለወልድም ፡ ሕይወት ፡ ይኖረው ፡ ዘንድ ፡ ሕይወትን ፡ ሰጠው ፤ እስመ ፡ ወልደ እግዚአብሔር ፡ ወልደ ፡ እጓለ ፡ እመሕያው ፡ ውእቱ ፡ (የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ የሰው ፡ ልጅ ፡ ነውና))” ፡ እንዳለ ፡ ወንጌለ ፡ ዮሐንስ(ምዕ ፡ 5t 26) ፡፡
ወልድ ፡ እምቅድመ ፡ ዓለም ፡ በመለኮቱ ፡ ከአብ ፡ ሲወለድ ፡ በባሕርየ ፡ መለኮት ፡ መቀበል ፡ የለበትምና ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስን ፡ ተቀብሎ ፡ ተወለደ ፡ ይሉት ፡ ዘንድ ፡ አይገባም ፤ ዛሬ ፡ ግን ፡ በሥጋ ፡ ርስት(በሥጋነቱ) ፡ መቀበል ፡ አለና ፡ የባሕርይ ፡ ሕይወቱ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስን ፡ ተቀብሎ ፡ ከአብ ተወለደ ፡ ይባላል ፡ እንጅ ፡፡ “መኑ ፡ ውእቱ ፡ ወልዱ ፡ ዘተወፈየ ፡ ኵነኔ ፡ አብ ፡ እንበለ ፡ ሥጋሁ ፡ ወአኮ ፡ መለኮቱ ፤ ወመለኮትሰ ፡ ኢይትወፈይ ፡ ኵነኔ ፡ ወኢይነሥእ ፡ ሥልጣነ ፡ እመለኮት ፤ ወኢይሰይሞ ፡ መለኮት ፡ ለመለኮት (የፍትረትን ፡ ሁሉ ፡ ፍርድ ፡ የተቀበለ ፡ ልጁ ፡ ማን ፡ ነው? ፡ ከሥጋው ፡ መለኮትም ፡ አይደል ፡ መለኮትስ ፡ ፍርድን ፡ አይቀበልም ፡ ሥልጣንንም ፡ ከመለኮት ፡ አይወስድም ፡ መለኮትን ፡ መለኮት ፡ አይሾመውም)” ፡ እንዳሉ ፡ ሊቃውንት ፡ በመዝገበ ፡ ሃይማኖት(አንቀጽ ፡ 1 ፡ ቁ 35-36) ፡፡
እነሆ ፡ ዛሬ ፡ የዚህ ፡ ዓለም ፡ ልጅ ፡ እገሊት ፡ እናትህ ፤ እገሊት ፡ አባትህ ፡ ነው ፡ ካላሉት ፡ አባት ፡ እናቱን ፡ አየውቅም ፡፡ እንደዚህም ፡ ሁሉ ፡ ወልድ ፡ “እግዚአብሔር ፡  ይቤለኒ ፡ ወልድየ ፡ አንተ ፡ ወአነ ፡ ዮም ፡ ወለድኩከ( እግዚአብሔር ፡ አለኝ ፡ አንተ ፡ ልጄ ፡ ነህ ፡ እኔ ፡ ዛሬ ፡ ወለድኩህ)” ፡ ማለቱ ፡ ወልድ ፡ ከአብ ፡ እንደተወለደ ፡ የማያውቅ ፡ ሁኖ ፡ አብ ፡ ነግሮት ፡ ነውን?ቢሉ ፤ እንደዚህስ ፡ አይደለም ፡ ይልቁንም ፡ ለሐዋርያት ፡ ያልጠየቁትን ፡ ምሥጢር ፡ ሲነግራቸው ፡ እንጅ ፡ ነው ፡፡ ማለትም ፡ አብ ፡ ለሐዋርያት ፡ ሲያስተምር ፡ ለወልድ ፡ የነገረ ፡ እየመሰለ ፡ ያስተምራቸዋል ፡፡ ሐዋርያት ፡ ግን ፡ ኋላ ፡ እየጠየቁ ፡ ይረዱታል ፤ ይህም ፡ ይታወቅ ፡ ዘንድ ፡ ዓርብ ፡ ሊሰቀል ፡ በምሴተ ፡ ሐሙስ ፡ “አባ ፡ ቅዱስ ፡ ዕቀቦሙ ፡ በስምከ” ፡ ብሎ ፡ ጸለየላቸው ፡፡ ሐዋርያት ፡ “ዕቀቦሙ” ፡ እየአለ ፡ የሚጸልይልን ፡ ከዚህ ፡ ዓለም ፡ በሞት ፡ ውሰዳቸው ፡ ሲል ፡ ነው ፡ ብለው ፡ ጌታን ፡ ጠረጠሩት ፤ ጌታም ፡ ቢጠረጥሩት ፡ “ወኢይብለከ ፡ ከመ ፡ ትንሥኦሙ ፡ እምዓለም ፡ ዳዕሙ ፡ ከመ ፡ ትዕቀቦሙ ፡ እምእኩይ” ፡ ብሎ ፡ ጸለየላቸው ፡ እኩያን ፡ የተባሉ ፡ አጋንንት ፡ መናፍቃን ፡ ናቸው ፡ “ዕቀቦሙ” ፡ ማለቴም ፡ ከፍትወታተ ፡ እኩያት ፡ ከኃጣውእ ፡ ርኩሳት ፡ ጠብቃቸው ፡ ስልህ ፡ ነው ፡ እንጅ ፡ ከዚህ ፡ ዓለም ፡ በሞት ፡ ውሰዳቸው ፡ ስልህ ፡ አይደለም ፤ ብሎ ፡ ወልድ ፡ ለአብ ፡ የነገረው ፡ መሰለ ፤ ይህንን ፡ ጊዜ ፡ ወልድ ፡ “ዕቀቦሙ” ፡ ብሎ ፡ የጸለየውን ፡ ለሕይወት ፡ እንጅ ፡ ለሞት ፡ እንዳልሆነ ፡ አብ ፡ የማያውቅ ፡ ሆኖ ፡ ወልድ ፡ ነግሮት ፡ አይደለም ፡ ለሐዋርያት ፡ ለማስረዳት ፡ ነው ፡ እንጅ ፡፡ እንደዚህም ፡ ሁሉ ፤ “አንተ ፡  ልጄ ፡ ነህ ፤ ዛሬ ፡ ወድኩህ ፡ አለኝ” ፡ ማለቱ ፤ እምቅድመ ፡ ዓለም ፡ በመለኮቱ ፡ የባሕርይ ፡ ልጅነት ፡ ያለው ፡ ሲሆን ፡ ልጅነትን ፡ ስለሚሻ ፡ ስለ ፡ ሥጋ ፡ እንግድነት ፡ ዛሬ(በጊዜ ፡ ተዋሕዶ)  ፡ በሰውነቱ ፡ ከአብ ፡ የባሕርይ ፡ ልደት ፡ መወለዱን ፡ ሲያጠይቅ ፣ ለሐዋርያት ፡ ሲነግራቸው ፡ እንጅ ፡ የማያውቅ ፡ ሁኖ ፡ አብ ፡ ነግሮት ፡ አይደለም ፡፡

Saturday, December 22, 2018

የሥሉስ ፡ ቅዱስ ፡ ህልውና

በስመ ፡ አብ ፡ ወወልድ ፡ ወመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ 

አሐዱ ፡ አምላክ

የሥሉስ ፡ ቅዱስ ፡ ህልውና
ዛሬ ፡ የምንመለከተው ፡ ሥላሴ ፡ በህልውና(በአነዋወር) ፡ አንዴት ፡ እንደሆኑና ፤ ቤተ ፡ አይሁድ ፡ ካሮች ፡ ሳይረዱት ፡ ሳያውቁት ፡ ብዙ ፡ ክርስቶሳውያንን ፡ ሁለተኛ ፡ እያጠመቅ ፡ አይሁድ ፡ አረሚ ፡ ለሚያደርጉበት ፡ የክሕደት ፡ ቃል ፡ ፍቱን ፡ መድኃኒት ፡ የሚሆን ፡ መልእክትን ፡ ይሆናል ፤ ይህንን ፡ ቃልም ፡ የጻፍኩላችሁ ፡ ቤተ ፡ አይሁድ ፡ ኬልቄዶናውያን ፡ እቤታቸው ፡ ታቅፈውት ፡ ከሚገኘው ፡ አክሲማሮስ ፡ ከተባለ ፡ የብራና ፡ መጽሐፋቸው ፡ ነው ፡፡ =============================================
የሥላሴ ህልውና እንዴት ነው እንደምን ይኖራሉ ቢሉ ፤ እንደ አንድ ሰው ይኖራሉ ፡፡ የ1ሰው ኑሮው እንዴት ነው ቢሉ ፤ በልቡ አስቦ በቃሉ ተናግሮ በእስትንፋሱ ተንፍሶ ደኅና ሁኖ ይኖራል ፡፡ በልቡ ሲያስብ ቃሉና እስትንፋሱ አይለዩም ፤ በቃሉም ሲናገር ልቡናው እስትንፋሱ አይለዩም ፡፡ ሥላሴም እንዲህ ናቸው ፡፡ ሰው ቃሉ እስትንፋሱ ሳይለየው በልቡ አስቦ ደኅና ሁኖ እንዲኖር ወልድና መንፈስ ቅዱስም ለባውያን በአብ ናቸው ፤ በአብ ያስባሉ ፤ ለወልድና ለመንፈስ ቅዱስ ልባቸው አብ ነው ፤

Thursday, December 20, 2018

በተዋሕዶ ከበረ ባዮች ምንፍቅና በሊቃውንት መጽሐፍ[በዝክሪ ወጳውሊ ዘደብረ ጽሞና መጽሐፍ]




“የዘማርያን ምንፍቅናና የካሮች[በተለምዶ ተዋሕዶ ብለው ራሳቸውን የሚጠሩ] አስተምህሮ በምስራቅ ጎጃም በምትገኘው ደብረ ጽሞና ገዳም ይኖሩ በነበሩትና ካቶሊካውያንን ተከራክረው የቅዱሳን አበውን ትክክለኛዋን አስተምህሮ ያቆዩልን አባ ዝክሪና አባ ጳውሊ ከሚባሉት ሊቃውንት መጽሐፍ ላይ ተቀንጭቦ የተወሰደ”
~~~~~~~~~~~~//~~~~~~~~~~~~~//~~~~~~~~~~~~~~~
“በአለም ሰገድ በመንግስቱ ዘመን በነገሰ በአስራ አምስት ዓመቱ ክርስቶስ ቀባዒና ተቀባዒ ቅብዕ የሚል ስሙ ዘማርያን የተባለ መናፍቅ ዳግመኛ ተነሳ:: ይሄውም ዘማርያን 
ጀርማናዊው ደቀ መዝሙር ነበር ከእርሱም ትርጓሜውን ሰማ እንደ መምህሩም ሆነ ክርስቶስ ቀባዒና ተቀባዒ ቅብዕ ነው እያለ ያስተምር ጀመር፤
.......ምዕመናንም ሰሙት ምዕመማንም ይህን ትምህርትና ይህን ሃይማኖት ማን አስተማረህ አሉት:: 

.......መናፍቁ ዘማርያንም መለሰ ጌታችን በወንጌሉ እኔ በአብ አብ በእኔ እኔና አብ አንድ ነን ያለውን እርሱ ምስክሬ ነው አላቸው:: እኔም ይህን ነገር አውቄ አብ ከወልድ ጋር ካለ ስለዚህ ክርስቶስ ሌላ ቀባዒና ቅብዓትን አይፈልግም እርሱ ቀባዒ እርሱም ተቀባዒ እራሱም ቅብዕ ነው እላለሁ አለ:: 

Monday, December 17, 2018

ወልደ ፡ አብ ፡ በወልደ ፡ አብ : ክፍል ፡ ሦስት

ወልደ ፡ አብ ፡ በወልደ ፡ አብ : ክፍል ፡ ሦስት
==================================
የጌታችን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅነት ፡ እና


የቤተ ፡ አይሁድ ፡ ካሮች ፡ ውድቀት
======================================
በባለፈው ፡ መልእክት ፡ ቤተ ፡ አይሁድ ፡ ካሮች ፡ ለእመቤታችን ፡ የምንሰግደው ፡ ስግደት ፡ የወልደ ፡ እግዚአብሔር ፡ የባሕርይ ፡ ልጅነት ፡ ያጠይቃል ፡ በሚለው ፡ ሀሳብ ፡ ዙሪያ ፡ ላይ ፡ በሰፊዉ ፡ ተነነጋግረናል ፡፡ እኒህ ፡ ቤተ ፡ አይሁድ ፡ ካሮች ፡ ነጠላ ፡ ቃል ፡ እየመዘዙ ፡ ራሳቸውን ፡ ከጥልቅ ፡ ጉድጓድ ፡ ሲገቡ ፡ ይስተዋላሉ ፡፡ “ለመስቀል ፡ መሰገዱ ፡ የእሱን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅነት ፡ ያጠይቃል ፡ እንዴት ፡ ቢሉ ፤ እንግዲያው ፡ የቅዱስ ፡ ጴጥሮስ ፡ የቅዱስ ፡ ጊዮርጊስ ፡ መስቀል ፡ ይሰገድለታልን ፤ ስንኳንስ ፡ ለመስቀሉ ፡ ለርሳቸው ፡ አይሰገድላቸውም ፤መስቀል ፡ ግን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅ ፡ የሆነው ፡ ሥጋው ፡ ቢፈስበት ፤ ደሙ ፡ ቢፈስበት ፡ እሰግድ ፡ ለመስቀለ ፡ እግዚእነ ፡ ኢየሱስ ፡ ክርሰቶስ ፡ ዘተቀደሰ ፡ በደሙ ፡ ክቡር” ፡ ብለን ፡ እንሰግድለታለን›››››››ወልደ ፡ አብ ፡ ገፅ ፡ 251 ፤ ተብሎ ፡ የተቀመጠውን ፡ ቃል ፡ ሙሉውን ፡ ሳይቀበሉና ፡ ሳይመለከቱ ፡ “ስንኳንስ ፡ ለመስቀሉ ፡ ለርሳቸው ፡ አይሰገድላቸውም” ፡ የምትለዋን ፡ ቁንጽል ፡ ሀሳብ ፡ እያነሱ ፡ ለመስቀል ፡ አይሰገድም ፡ ለጻድቃንም ፡ አይሰገድም ፡ ብላችኋል ፡ እያሉ ፡ የጅል ፡ ንግግር ፡ ይናገራሉ ፤ ራሳቸው ፡ ቈናጽላን ፡ መሆናቸውን ፡ እንኳን ፡ አልተረዱም ፡፡ እነሱ ፡ እድሜ ፡ ልካቸውን ፡ እንደዚህ ፡ ይላሉ ፣ አከሌ ፡ ተሐድሶ ፡ ነው ፣ እሌ ፡ መናፍቅ ፡ ነው …..ሌላም ፡ ሌላም ፡ እያሉ ፡ የሰው ፡ ስም ፡ መስበር ፡ እንጅ ፡ የእነሱ ፡ ክሕደትና ፡ ውድቀት ፡ አይታያቸውም ፡፡ ሲያሻቸው ፡ ቅብዐት ፡ የሚለውን ፡ ተዋሕዶ ፡ እያሉ ፡ በነሲብ ፡ በመተርጐም ፣ ሲያሻቸው ፡ ተቀብዐ ፡ የሚሉ ፡ ቃላትን ፡ ከቅዱስ ፡ መጽሐፍ ፡ እየቆረጡ ፡ በማውጣት ፣ ሲያሻቸው ፡ ደግሞ ፡ የዋሁን ፡ ምእመን ፡ እንዲህ ፡ ቁንጽልጥል ፡ እያደረጉ ፡ እያወጡ ፣ ሲያሻቸው ፡ ደግሞ ምንጭ ፡ የሌለው ፡ አሉባልታና ተረት ፡ ተረት ፡ አንዲት ፡ ጥቀትን ፡ ሁለተኛ ፡ እያጠመቅ ፡ እያደሱ ፡ ሌላውን ፡ ተሐድሶ ፡ እያሉ ፡ ይሳደባሉ ፤ ክርስቲያኖችንም ፡ እስላ ፡ አረሚ ፡ አይሁድ ፡ ከሐዲ ፡ ያደርጋሉ ፡፡ ልቡና ፡ ያላችሁ ፡ ሁላሁም ፡ እኔ ፡ ዘወትር ፡ የሚያንገበግበኝና ፡ ሥራየን ፡ ሁሉ ፡ ትቼ ፡ የምጽፍላችሁ ፡ ሥልጣን ፡ አስፈልጎኝ ፤ አልያም ፡ የምሠራው ፡ ሥራ ፡ ስለሌለኝ ፡ ተረ ፡ ረብ ፡ ጥቅም ፡ ማግኘት ፡ ፈልጌ ፡ ሳይሆን ፤ እውነትን ፡ እያየሁ ፡ ብዙዎች ፡ ሲቀብሯት ፡ ዝም ፡ ማለት ፡ ስለሌለብኝ ፡ ነው ፡፡ ለምድዊ ፡ ድሎትና ፡ ምቾት ፡ አምላክ ፡ በቸርነቱ ፡ ለደመወዝ ፡ የምትሆን ፡ ሥራ ፡ ሰጥቶኝ ፡ እኔንም ፡ ቤተሰቤንም ፡ በፈጣሪ ፡ ቸርነት ፡ እያኖርኩባት ፡ ነው ፡፡  

Friday, December 14, 2018

ወልደ ፡ አብ ፡ በወልደ ፡ አብ : ክፍል ፡ ሁለት

ወልደ ፡ አብ ፡ በወልደ ፡ አብ : ክፍል ፡ ሁለት
==================================
የጌታችን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅነት ፡ እና


የቤተ ፡ አይሁድ ፡ ካሮች ፡ ውድቀት
======================================
በገዛ ፡ ሥልጣኔ ፡ ተነሣሁ ፡ ሲል ፡ ለወልድ ፡ ከአብ ፡ ከመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ የተለየ ፡ ሥልጣን ፡ አለውና ፡ በተለየ ፡ ሥልጣኔ ፡ ተነሣሁ ፡ ሲል ፡ ነውን? ፡ ቢሉ ፤ ከአብ ፡ ከመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ጋር ፡ በሥልጣን ፡ ዕሪናውን ፡ ሲያጠይቅ ፡ እጅ ፡ የተነሣስ ፡ በ3ቱም ፡ ሥልጣን ፡ ነው ፡፡ “አማን ፡ በአማን ፡ ተንሥአ ፡ እሙታን ፡ በኃይለ ፡ አቡሁ ፡ ወመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ በሥልጣኑ ፡ ፈቲሆ ፡ ማዕሠሮ ፡ ለሞት()” ፡ እንዳለ ፡ ድርሳነ ፡ ማኅየዊ() ፡፡ በ3ቱም ፡ ሥልጣን ፡ እንደተነሣ ፡ ሊቃውንቱ ፡ በዝርዝር ፡ ተናረዋል ፡፡
በአብ ፡ ሥልጣን ፡ እንደተነሣ ፡ ቅዱስ ፡ ጳውሎስ ፡ “አብ ፡ አንሥኦ ፡ ለወልዱ ፡ እሙታን” ፡ ብሏል ፡፡ በገዛ ፡ ሥልጣኑ ፡ እንደተነሣ ፡ ቅዱስ ፡ ቄርሎስ ፡ “ወተንሣእኩ ፡ በሥልጣነ ፡ ባሕቲትየ” ፡ ብሏል ፡፡ በመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ሥልጣን ፡ እንደተነሣ ፡ ባስልዮስ ፡ ዘቂሣርያ ፡ “ወተንሥአ ፡ በኃይለ ፡ መለኮቱ”  ፡ ብሏል(ሃይ.አበው ፡ ምዕ ፡ 34 ፡ ክ ፡ 5 t18) ፡፡ ኃይል ፡ የተባለ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ እንደሆነ ፡ ለማጠየቅ ፡ ወንጌለ ፡ ሉቃስ(ምዕ ፡ 24t49) ፡ “ወናሁ ፡ እፌኑ ፡ ተስፋሁ ፡ ለአቡየ(እኔም ፡ ተስፋ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስን ፡ እልክላችኋለሁ) ፡ ወአንትሙሰ ፡ ንበሩ ፡ ሀገረ ፡ ኢየሩሳሌም ፡ እስከ ፡ ትለብሱ(እናንተ ፡ ግን ፡ ከሰማይ ፡ ሀይልን ፡ ማለት ፡ ሰማያዊ ፡ ሀብትን ፡ እስክትለብሱ ፡ በኢየሩሳሌም ፡ ኑሩ)” ፡ ብሏል ፡፡ይህስ ፡ ይሁን ፡ በሥልጣነ ፡ ባሕቲትየ ፡ ማለቱ ፡ በብቻየ ፡ ሲል ፡ አይደለምን? ፡ ቢሉ ፤ ይህስ ፡ ትንሣውን ፡ ሲያይ ፡ የተናረው ፡ ነው ፡፡ ማለትም ፡ አብና ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ እንደሱ ፡ ሰው ፡ አልሆኑም ፤ እሱ ፡ ግን ፡ ሰው ፡ የሆንኩ ፣ ከሙታን ፡ የተነሣሁ ፡ በተለየ ፡ አካሌ ፡ እኔ ፡ ብቻ ፡ ነኝ ፡ ሲል ፡ “ወተንሣእኩ ፡ በሥልጣነ ፡ ባሕቲትየ” ፡ አለ ፡ እንጅ ፡ ከአብና ፡ ከመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ የተለየ ፡ ሥልጣን ፡ አለኝ ፡ ሲል ፡ አይደለም ፡፡
ዳግመኛም ፡  የጸጋ ፡ ልጅ ፡ የግድ ፡ ይታመማል ፣ የግድ ፡ ይሞታል ፡ እንጅ ፡ በፈቃዱ ፡ አይታመምም ፣ በፈቃዱ ፡ አይሞትም ፤ እርሱ ፡ ግን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅ ፡ ነውና ፡ በፈቃዱ ፡ ታመመ ፡ ሞተ ፤ “ሞተ ፡ በፈቃዱ ፡ ወተቀብረ ፡ በሥምረቱ” ፡ እንዳለ ፡ ዮሐንስ ፡ ነባቤ ፡ መለኮት ፡፡ ዳግመኛም ፡ የጸጋ ፡ ልጅ ፡ የራሱን ፡ ይታመማል ፡ ይመሞታል ፤ “እመሰ ፡ ኀደረ ፡ ቃል ፡ ላዕሌሁ ፡ ከመ ፡ ኵሎሙ ፡ ነቢያት ፡ ለምንትኑ ፡ ኢተብህለ ፡ በእንተ ፡ ግብሮሙ ፡ እምልደቶሙ ፡ እስከ ፡ ዕለተ ፡ ሞቶሙ ፡ ኮነ ፡ በእንቲአነ ፡ አላ ፡ በእንተ ፡ ርእሶሙ ፡ ባሕቲቶሙ(በነቢያት ፡ ሁሉ ፡ እንዲያድር ፤ ቃል ፡ ከአደረበት ፡ ከተወለዱ ፡ ጀምሮ ፡ እስከ ፡ ሞታቸው ፡ ድረስ ፡ የሠሩት ፡ ሥራ ፡ እኛን ፡ ለማዳን ፡ ተደረገ ፡ ለምን ፡ አልተባለም? ፡ ራሳቸውን ፡ ብቻ ፡ ለማዳን ፡ እንደሆነ ፡ ተነገረ ፡ እንጅ ፡፡  
እመሰ ፡ ኀደረ ፡ ላዕሌሁ ፡ ቃል ፡ ከመ ፡ ኩሎሙ ፡ ነቢያት(በነቢያት ፡ ሁሉ ፡ እንዲያድር ፡ ቃል ፡ ከአደረበት) ፤ ለምንትኑ ፡ ተብህለ ፡ በእንተ ፡ ዝንቱ ፡ ባሕቲቱ ፡ ዘተወልደ ፡ እምእግዝእትነ ፡ ቅድስት ፡ ድንግል ፡ ማርያም ፡ ምዕረ ፡ ቦአ ፡ ውስተ ፡ ዓለም ፡ በደኃሪ ፡ መዋዕል(ከእግዝእትነ ፡ ማርያም ፡ ስተወለደ ፡ ስለእርሱ ፡ ብቻ ፡ 5500 ፡ ዘመን ፡ ሲፈጸም ፡ አንድ ፡ ጊዜ ፡ ሰው ፡ ሁኖ ፡ ተወለደ ፡ ተብሎ ፡ ለምን ፡ ተነገረ)” ፡ እንዳለ ፡ አትናቴዎስ(ሃይ.አበው ፡ ምዕ ፡ 31t31-32) ፡፡ ጌታ ፡ ግን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅ ፡ የባሕርይ ፡ አምላክ ፡ ነውና ፡ ለሰው ፡ ብሎ ፡ ታመመ ፡ ሞተ ፤ “ሞተ ፡ ከመ ፡ ያሕይዎሙ ፡ ለምውታን” ፡ እንዳለ ፡ ዮሐንስ ፡ ነባቤ ፡ መለኮት ፡፡
ምነዋ ፡ የጸጋ ፡ ልጆች ፡ ጻድቃን ፣ ሰማዕታት ፡ መታመማቸው ፣ መሞታቸው ፡ በፈቃዳቸው ፡ አይደለምን?፡ እንደምን ፡ የግድ ፡ ይሆናል? ፡ ቢሉ ፡ ጌታ ፡ ሲአስተምር ፡ በወንጌለ ፡ ማቴዎስ(ምዕ ፡ 1t36) ፡ ላይ ፡ “ዘኢሐደገ ፡ አባሁ ፡ ወእሞ ፣ ቤቶ ፡ ወዉሉዶ ፡ ወዘኢፆረ ፡ መስቀለ ፡ ሞትየ ፡ ኢይክል ፡ ይፀመደኒ” ፡ ብሎ ፡ እንደገለጸው ፤ እናት ፡ አባቱን ፣ ቤት ፡ ንብረቱን ፡ ትቶ ፡ እኔን ፡ ያልተከተለ ፡ ከእኔ ፡ አንድነት ፡ የለውም ፡ መንግሥተ ፡ ሰማያትን ፡ እንኳንስ ፡ ሊገባባት ፡ አያያትም ፡ ብሎ ፡ አዋጅ ፡ ተናግሯል ፡፡ ጻድቃን ‹ ሰማዕታትም ፡ ይህ ፡ አዋጅ ፡ ግድ ፡ ብሏቸው ፡ ይታመማሉ ፡ ይሞታሉ ፡ እንጅ ፡ በፈቃዳቸው ፡ አይታመሙም ፡ አይሞቱም ፤ እሱ ፡ ግን ፡ ይጸድቅበታል ፡ እንዳይባል ፡ በባሕርዩ ፡ ጻድቅ ፤ ይብርበታል ፡ እንዳይባል ፡ የባሕርይ ፡ ክቡር ፡ ነውና ፡ ለሰው ፡ ሲል ፡ በፈቃዱ ፡ ታመመ ፡ ሞተ ፡:

Wednesday, December 12, 2018

ወልደ ፡ አብ ፡ በወልደ ፡ አብ ክፍል ፡ አንድ


የጌታችን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅነት ፡ እና ፡


የቤተ ፡ አይሁድ ፡ ካሮች ፡ ውድቀት
======================================
ወንድሞች ፡ እህቶች ፡ እንደምን ፡ አላችሁልኝ?ሕይወት ፡ እንዴት ፡ ነው?ሁሉም  ሠላም?አምላክ ፡ ይመሥገን ፡፡ የዛሬው ፡ መልእክቴ ፡ የሚያተኩረው ፡ በቅርቡ ፡ አንዳንድ ፡ ወንድሞች ፡ “እናንተ ፡ ቅብዐቶች ፡ ለመስቀልና ፡ ለጻድቃን ፡ ስግደት ፡ አይገባም ፡ ብላችሁ ፡ ጽፋችኋል ፡ በመጽሐፋችሁ” ፡ እያሉ ፡ ሲከሱን ፡ ሲወቅሱን ፡ አስተውያለሁ ፡፡ የቅብዐቱን ፡ ጣዕመ ፡ ምሥጢር ፡ ሳያውቁት ፡ በልካችን ፡ እያበዙ ፡ አንድ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስን ፡ ሲበዘብዙት ፡ ብንመለከትም ፡ የፍርዱ ፡ ባለቤት ፡ አምላክ ፡ እሱ ፍርዱን ፡ ያስቀምጣል ፡ ፡ ማቴ 12፡ 32 ፤ ብዙ ፡ ወንድሞችና ፡ እህቶችንም ፡ በዚህ ፡ ቃል ፡ ምክንያት ፡ ድጋሚ ፡ አጥምቀው ፡ እስላም ፡ አረሚ ፡ አድርገውበታል ፤ እያደረጉበትም ፡ ይገኛል ፡፡ ስለዚህ ፡ እውነታው ፡ ምን ፡ እንደሆነ ፡ መጻፍ ፡ ስላለብኝ ፡ ከመጽሐፉ ፡ ያለውን ፡ ቃል ፡ ሳልጨምር ፡ ሳልቀንስ ፡ እንዲህ ፡ አርበዋሁ፡፡ አንብብዋ ፡ ለመልእት ፡ እምጥታ ፡ እስከ ተፍጻሜታ ፤ እንዲሉ ፤ ከመጀመሪያው ፡ እስከመጨረሻው ፡ ሳያነቡ ፡ የወደቁት ፡ ካሮች ፡ እኛን ፡ ማላመጥ ፡ አፋቸውን ፡ መፍቻ ፡ ስላደረጉት ፡ ነው ፡ እንጅ ፤ በወልደ ፡ አብ ፡ ላይ ፡ የተገለጠው ፡ ቃል ፡ ለቅዱሳንና ፡ ለመስቀል ፡ ስግደት ፡ አያስፈልግም ፡ የሚል ፡ አይደለም ፡፡ ስለሆነም ፡ የመጽሐፉን ፡ ሙሉ ፡ ኃይለ ፡ ቃል ፡ እንደሚከተለው ፡ ላስነብባሁ፡፡

Thursday, December 6, 2018

ወልድ በሥጋው ሞተ እንደተባለ በሥጋው ፍጡር እንደሚባል የአበው ምስክር




፩ኛ............  “ወንነጽር  ለለ፩ዱ ቃል እምቃላት ወኃይለ ዘውስቴቶሙ ወንትናገር ዳግመ ምክንያተ ነገር ዘይቤልዎ ዘከመ ትስብእቱ ናሁ ------ ከመጽሐፍት ቃላት እያንዳንዱን ቃላት በውስጣቸውም ያለውን ምስጢር እናስተውል፤ ሰው እንደመሆኑ የተነገሩለትን፤ የነገሩንም ምክንያት ዳግመኛ እንናገር::  ዮሐ 5፥39 ፤
 ናሁ አቅደምነ ወተናገርነ ባህሎ  ዘይቤ አምላኪየ ዘውእቱ አምላክክሙ ብዙኃ ጊዜያተ ከመ ይለቡ ዘአልቦቱ አእምሮ ፍናወ ፩ዱ ቃል ወዘተብህለ ከመ ውእቱ ሰብእ ወአልቦ ዘየአምሮ----  ይኸውም ፈጣሪያችሁ ነው፤ እነሆ አምላኪየ ያለበትን ነገር አስቀድመን መላልሰን ተናግረናልና፤ ሰው  እንደሆነ የሚያውቀውም እንደሌለ የተናገረለትን እያንዳንዱን ቃል መንገድ (ምስጢር) ዕውቀት የሌለው ሰው ያውቅ ዘንድ ፤
  ወበዝንቱ ቃለ መጽሐፍ ቅዱስ ይትዐወቅ ከመ ውእቱ እም፪ቱ ዘያስተርኢ ወዘኢያስተርኢ ፩ዱ ሕላዌ በእንተሰ ዘያስተርኢ ይቤ አምላኬየ ወበእንተ ዘያስተርኢ ይቤ አቡየ ---- በዚህም በቅዱሳት መጽሐፍት ቃል እርሱ ከሚታየውና ከማይታየው ከሁለቱ አንድ አካል አንድ ባሕርይ እንደሆነ ይታወቃል፤ ስለ ክበበ ትስብእት አምላኪየ አለ ስለ መለኮት አባቴ አለ::
ወአልቦ ዘይክል መኑሂ ያውሥእ ቃለ በእንተ እሉ ፪ቱ ሥርዓታት እፎኑ ውእቱ ሰብእ ዘኢኮነ ፍጡረ  ወለእመ ኢኮነ ሰብአ እፎመ ተሰምየ ሰብአ ---- አባቴ አምላኪየ ስለ አላቸው ስለ እነዚህ ምስጢራት መልስ ሊሰጥ የሚችል የለም፤ ፍጡር ያይደለ ሰው እንደምን ያለ ነው? ሰውስ ካልሆነ እንዴት ሰው ይባላል? ” ሃይ/አበው  ዘኤጲፋንዮስ ምዕ 54፥16 – 19 ይላል::
፪ኛ........... “ወዘሰ ንቤ ፍጡር ውእቱ በእንተ ዘተሣተፈ ሥጋ ድካምነ በሥርዓት ዘገብሮ በእንቲአነ-- ፍጡር[ሰው] ነው ያልነውም ስለ እኛ ባደረገው ተዋሕዶ ደካማ ባሕርያችንን ስለተዋሐደ ነው” ሃይ/ አበው ዘጎርጎርዮስ 35፥3

Wednesday, December 5, 2018

በእውኑ ቅዱስ ቄርሎስ ቅብዓትን አውግዟልን?

በተለምዶ ተዋሕዶዎች ተብለው የሚጠሩ ትክክለኛ ስማቸው ግን ካሮች መሲሕ በመንፈሰ አቡሁ ብለን የምናምነውንና መሲሐዊያን፣ ቅብዓን፣ ናዝራዊያን ተብለን የምንጠራውን እኛን ለማጭበርበር ሲፈልጉ ቅብዓትን እኮ ቅዱስ ቄርሎስ አውግዞታል ይሉናል:: እውነታውን ግን አብረን እንየው:- 
ብዙዎቹ በተዋሕዶ ከበረ ብለው የሚያምኑ ሰዎች “ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በእርሱ አጋዥነት ድንቅ ተአምራትን ያደርግ ዘንድ በመንፈስ ቅዱስ ከበረ የሚለው ፤ ርኩሳን አጋንንትን በማውጣት ጊዜም ኃይልን ተአምራትን ከመንፈስ ቅዱስ ይቀበላል በሰውም የአምላክነትንም ሥራ እርሱ ራሱ ይሠራል የማይል ቢኖር ውጉዝ ይሁን ሃይ/ አበው ዘቄር 73÷49” በማለት አውግዟችኋል ይሉናል::

Monday, December 3, 2018

እውነት አለቀሰች






                                                   ልብ ያለህ አስተውል፣ ጆሮ ያለህ ስማ፣
                                  እግርህ እንዳይገባ ከክህደት ከተማ::
                                  የያዝከውን አጽና ልብህ አይጨነቅ፣
                                  ለጥያቄህ መልስም ሊቃውንትን ጠይቅ::
                                  ለእውነት የቆመ ሃይማኖቱን የሚያውቅ፣
                                  ንባብ ትርጓሜን ጠንቅቆ የሚዘልቅ፣
                                  ተናገር ዮሐንስ አንተ ልሳነ ወርቅ::