Monday, December 17, 2018

ወልደ ፡ አብ ፡ በወልደ ፡ አብ : ክፍል ፡ ሦስት

ወልደ ፡ አብ ፡ በወልደ ፡ አብ : ክፍል ፡ ሦስት
==================================
የጌታችን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅነት ፡ እና


የቤተ ፡ አይሁድ ፡ ካሮች ፡ ውድቀት
======================================
በባለፈው ፡ መልእክት ፡ ቤተ ፡ አይሁድ ፡ ካሮች ፡ ለእመቤታችን ፡ የምንሰግደው ፡ ስግደት ፡ የወልደ ፡ እግዚአብሔር ፡ የባሕርይ ፡ ልጅነት ፡ ያጠይቃል ፡ በሚለው ፡ ሀሳብ ፡ ዙሪያ ፡ ላይ ፡ በሰፊዉ ፡ ተነነጋግረናል ፡፡ እኒህ ፡ ቤተ ፡ አይሁድ ፡ ካሮች ፡ ነጠላ ፡ ቃል ፡ እየመዘዙ ፡ ራሳቸውን ፡ ከጥልቅ ፡ ጉድጓድ ፡ ሲገቡ ፡ ይስተዋላሉ ፡፡ “ለመስቀል ፡ መሰገዱ ፡ የእሱን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅነት ፡ ያጠይቃል ፡ እንዴት ፡ ቢሉ ፤ እንግዲያው ፡ የቅዱስ ፡ ጴጥሮስ ፡ የቅዱስ ፡ ጊዮርጊስ ፡ መስቀል ፡ ይሰገድለታልን ፤ ስንኳንስ ፡ ለመስቀሉ ፡ ለርሳቸው ፡ አይሰገድላቸውም ፤መስቀል ፡ ግን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅ ፡ የሆነው ፡ ሥጋው ፡ ቢፈስበት ፤ ደሙ ፡ ቢፈስበት ፡ እሰግድ ፡ ለመስቀለ ፡ እግዚእነ ፡ ኢየሱስ ፡ ክርሰቶስ ፡ ዘተቀደሰ ፡ በደሙ ፡ ክቡር” ፡ ብለን ፡ እንሰግድለታለን›››››››ወልደ ፡ አብ ፡ ገፅ ፡ 251 ፤ ተብሎ ፡ የተቀመጠውን ፡ ቃል ፡ ሙሉውን ፡ ሳይቀበሉና ፡ ሳይመለከቱ ፡ “ስንኳንስ ፡ ለመስቀሉ ፡ ለርሳቸው ፡ አይሰገድላቸውም” ፡ የምትለዋን ፡ ቁንጽል ፡ ሀሳብ ፡ እያነሱ ፡ ለመስቀል ፡ አይሰገድም ፡ ለጻድቃንም ፡ አይሰገድም ፡ ብላችኋል ፡ እያሉ ፡ የጅል ፡ ንግግር ፡ ይናገራሉ ፤ ራሳቸው ፡ ቈናጽላን ፡ መሆናቸውን ፡ እንኳን ፡ አልተረዱም ፡፡ እነሱ ፡ እድሜ ፡ ልካቸውን ፡ እንደዚህ ፡ ይላሉ ፣ አከሌ ፡ ተሐድሶ ፡ ነው ፣ እሌ ፡ መናፍቅ ፡ ነው …..ሌላም ፡ ሌላም ፡ እያሉ ፡ የሰው ፡ ስም ፡ መስበር ፡ እንጅ ፡ የእነሱ ፡ ክሕደትና ፡ ውድቀት ፡ አይታያቸውም ፡፡ ሲያሻቸው ፡ ቅብዐት ፡ የሚለውን ፡ ተዋሕዶ ፡ እያሉ ፡ በነሲብ ፡ በመተርጐም ፣ ሲያሻቸው ፡ ተቀብዐ ፡ የሚሉ ፡ ቃላትን ፡ ከቅዱስ ፡ መጽሐፍ ፡ እየቆረጡ ፡ በማውጣት ፣ ሲያሻቸው ፡ ደግሞ ፡ የዋሁን ፡ ምእመን ፡ እንዲህ ፡ ቁንጽልጥል ፡ እያደረጉ ፡ እያወጡ ፣ ሲያሻቸው ፡ ደግሞ ምንጭ ፡ የሌለው ፡ አሉባልታና ተረት ፡ ተረት ፡ አንዲት ፡ ጥቀትን ፡ ሁለተኛ ፡ እያጠመቅ ፡ እያደሱ ፡ ሌላውን ፡ ተሐድሶ ፡ እያሉ ፡ ይሳደባሉ ፤ ክርስቲያኖችንም ፡ እስላ ፡ አረሚ ፡ አይሁድ ፡ ከሐዲ ፡ ያደርጋሉ ፡፡ ልቡና ፡ ያላችሁ ፡ ሁላሁም ፡ እኔ ፡ ዘወትር ፡ የሚያንገበግበኝና ፡ ሥራየን ፡ ሁሉ ፡ ትቼ ፡ የምጽፍላችሁ ፡ ሥልጣን ፡ አስፈልጎኝ ፤ አልያም ፡ የምሠራው ፡ ሥራ ፡ ስለሌለኝ ፡ ተረ ፡ ረብ ፡ ጥቅም ፡ ማግኘት ፡ ፈልጌ ፡ ሳይሆን ፤ እውነትን ፡ እያየሁ ፡ ብዙዎች ፡ ሲቀብሯት ፡ ዝም ፡ ማለት ፡ ስለሌለብኝ ፡ ነው ፡፡ ለምድዊ ፡ ድሎትና ፡ ምቾት ፡ አምላክ ፡ በቸርነቱ ፡ ለደመወዝ ፡ የምትሆን ፡ ሥራ ፡ ሰጥቶኝ ፡ እኔንም ፡ ቤተሰቤንም ፡ በፈጣሪ ፡ ቸርነት ፡ እያኖርኩባት ፡ ነው ፡፡  


  ወደቀደመ ፡ ሀሳቤ ፡ ልመለስና ፡ ካሮቹ ፡ ቆምጠው ፡ የሚያነሱትና ፤ ምእመናንን ፡ ለክሕደት ፡ የሚያቁበት ፡ ቃል ፡ በደንብ ፡ ሲብራራ ፤ ለመስቀል ፡ መሰገዱ ፡ የእሱን ፡ብየባሕርይ ፡ ልጅነቱን ፡ ያጠይቃል ፡ መባሉ ፡ ስለምን ፡ ነው? ፡ የቅዱስ ፡ ጊዮርጊስ ፣ የቅዱስ ፡ ጴጥሮስ ፡ መስቀል ፡ ይሰገድለት ፡ የለምን? ፡ የሚል ፡ ሰው ፡ ቢኖር ፡ እንኳንስ ፡ ለመስቀላቸው ፡ ለእነሱ ፡ አይሰገድላቸውም ፡፡ ለመስቀላቸው ፡ አይሰገድም ፡ መባሉ ፤ ጌታችን ፡ ለተሰቀለበት ፡ መስቀል ፡ ስንሰግድ ፡፡ “እሰግድ ፡ ለመስቀለ ፡ እግዚእነ ፡ ኢየሱስ ፡ ክርስቶስ ፡ ዘተቀደሰ ፡ በደሙ ፡ ክቡር” ፡ ብለን ፡ እንደሆነ ፡ ሁሉ ፤ ለነ ፡ ቅዱስ ፡ ጴጥሮስ ፡ መስቀል ፡ “እሰግድ ፡ ለመስቀለ ፡ ጴጥሮስ ፡ (ጊዮርጊስ) ፡ ብለን ፡ የምንሰግድ ፡ አይደለም ፡ ማለት ፡ ነው ፡፡ ምክንያቱም ፡ የእነሱ ፡ ደም ፡ መስቀሉን ፡ የሚቀድስ ፡ ሳይሆን ፡ የክርስቶስ ፡ ደም ፡ የፈሰሰበት ፡ በመሆኑ ፡ መስቀሉ ፡ እነሱን ፡ የሚቀደሳቸው ፡ ነውና ፡፡
 የጌታችን ፡ መስቀል ፡ ግን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅ ፡ የባሕርይ ፡ አምላክ ፡ ሥጋና ፡ ደም ፡ የፈሰሰበት ፡ ነውና ፡ “ዘተቀደሰ ፡ በደሙ ፡ ክቡር” ፡ ብለን ፡ መስገዳችን ፡ ክቡር ፡ ደም ፡ ያለው ፡ አምላካችን ፡ በመስቀል ፡ ላይ ፡ ሥጋውን ፡ ቈርሶ ፡ ደሙን ፡ አፍሶ ፡ እኛን ፡ ያዳነ ፡ መሆኑን ፡ የምንሰብክበት ፡ መሆኑን ፡ ያጠይቃልና ፡ ለመስቀል ፡ መሰገዱ ፡ የእሱን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅነት ፡ ያጠይቃል ፡ ማለት ፡ ስለዚህ ፡ ነው ፡፡ ለእሳቸው ፡ አይሰገድላውም ፡ መባሉ ፡ ደግሞ ፡ ለጌታችን ፡ የባሕርይ ፡ ስግደት ፡ እንድንሰግድ ፤ እንዲሁ ፡ ለጻድቃንም ፡ የባሕርይ ፡ ስግደት ፡ የምንሰግድ ፡ አይደለንም ፡ ማለት ፡ ነው ፡፡ ይልቁንም ፡ የጸጋ ፡ ስግደት ፡ እንሰግድላቸዋለን ፡ እንጅ ፡፡ ገና ፡ ለገና ፡ አይሰገድም ፡ ስለተባለ ፤ ለመስቀል ፡ እና ፡ ለቅዱሳን ፡ ስግደት ፡ አይገባቸውም ፡ ብሎ ፡ መደምደም ፡ ልክ ፡ ርጉም ፡ አርዮስ ፡ “ትቤ ፡ ጥበብ ፡ ፈጠረኒ” ፡ ያለውን ፡ ይዞ ፡ እንደካደ ፤ በዚህም ፡ ጫፍ ፡ ይዞ ፡ መነሳት ፡ ልማደ ፡ መናፍቃን ፡ ነውና ፡ አንድን ፡ ኃይለ ፡ ቃል ፡ የተጠቀሰበት ፡ ምሥጢር ፡ ምን ፡ እንደሆነ ፡ ሳያስተውሉ ፡ ድምዳሜ ፡ ላይ ፡ መድረስ ፡ ለስህተት ፡ የሚዳርግ ፡ ስለሆነ ፡ ልናስተውል ፡ ተገቢ ፡ ነው ፡፡  
በዚያውም ፡ ላይ ፡ መናፍቃን ፡ በሰውነቱ ፡ ለተሰቀለው ፡ በአምላክነቱ ፡ ይሰገድለታል ፡ የሚሉ ፡ ከሆነ ፤ በአምላክነቱ ፡ እንጅ ፡ በሰውነቱ ፡ ተወግቶ ፡ ከጐኑ ፡ በፈሰሰው ፡ ውኃ ፡ አንጠመቅም ፣ በሰውነቱ ፡ ሥጋውን ፡ በልተን ፡ ደሙን ፡ ጠጥተን ፡ አንድንም ፡ የሚሉ ፡ ያሰኛቸዋል ፡፡ አንድም ፡ እንደ ፡ ንሰጥሮስ ፡ ሁለት ፡ አካል ፡ ሁለት ፡ ባሕርይ ፡ ያሰኝባቸዋል ፡፡ “እለሰ ፡ የአምኑ ፡ በክልኤቱ ፡ ህላዌያት ፡ ያጌብሮሙ ፡ ለአሐዱ ፡ ይስግዱ ፡ ወለካልዑ ፡ ኢይስግዱ ፡ ይጠመቁ ፡ በዘመለኮት ፡ ወኢይጠመቁ ፡ በዘትስብእት(ሁለት ፡ አካል ፤ ሁለት ፡ ባሕርይ ፡ ብለው ፡ የሚያምኑ ፡ ለአንዱ ፡ እንዲሰግዱ ፡ ለአንዱ ፡ እንዳይሰግዱ ፤ በመለኮት ፡ ባሕርይ ፡ እንዲጠመቁ ፡ በሥጋ ፡ ባሕርይም ፡ እንዳይጠመቁ ፡ ግድ ፡ ይሆንባቸዋል)” ፡ እንዳለ ፡ አቡሊዲስ(ሃይ.አበው ፡ ምዕ ፡ 39 ፡  ክ ፡ 1t16)  ፡፡
ዮሐንስ ፡ ወንጌላዊ(ምዕ ፡ 1t14) ፡ ላይ ፡ “ወርኢነ ፡ ስብሐቲሁ ፡ ከመ ፡ ስብሐተ ፡ አሐዱ ፡ ዋሕድ ፡ ለአቡሁ(ለአባቱ ፡ እንደ ፡ አንድ ፡ ልጅ ፡ ክብር ፡ የሆነ ፡ ክብሩን ፡ አየን” ፡ ያለውን ፡ ሳዊሮስ ፡ ዘአንጾኪያ ፡ “አጠየቀነ ፡ ወንጌላዊ ፡ በመለኮቱ ፡ ወበትስብእቱ ፡ ከመ ፡ ወልድ ፡ ዋሕድ ፡ ለአቡሁ ፡ በብሂሎቱ ፡ ርኢነ ፡ ስብሐቲሁ ፡ ከመ ፡ ስብሐተ ፡ አሐዱ ፡ ዋሕድ ፡ ለአቡሁ (ወንጌላዊው ፡ ለአባቱ ፡ እንደ ፡ አንድ ፡ ልጅ ፡ ክብር ፡ የሆነ ፡ ክብሩን ፡ አየን ፡ ባለው በመለኮቱም ፡ በሰውነቱን ፡ ለአባቱ ፡ አንድ ፡ ልጅ ፡ እንደሆነ ፡ አስረዳን) ፡ ብሎ ፡ ተርጕሞታል ፡፡ እንዲህም ፡ ብሎ ፡ መተርጐሙ ፤ እምቅድመ ፡ ዓለም ፡ በመለኮቱ ፡ ድኅረ ፡ ዓለም ፡ በሰውነቱ ፡ ለአብ ፡ አንድ ፡ የባሕርይ ፡ ልጅ ፡ እንደ ፡ ሆነ ፡ ዮሐንስ ፡ ወንጌላዊ ፡ አስረዳን ፡ ሲል ፡ ነው ፡፡
ዛቲ ፡ ሃይማኖት ፡ መሲሐዊት ፡ ዘትትአመን ፡ ባቲ ፡ ቤተክርስቲያን ፡ ቅድስት
ምስጋና ፡ ለአንድ ፡ አምላክ ፡ ለቅድስት ፡ ሥላሴ
ክብር ፡ ለወላዲተ ፡ አምላክ ፡ ለድንግል ፡ ማርያም
ክብር ፡ ለመስቀለ ፡ ክርስቶስ ፡ እጸ ፡ መድኃኒት ፡ ኃይልነ ፡ ወጸወንነ

ወንድም ፡ እህቶች ፡ እኒህ ፡ ቤተ ፡ አይሁድ ፡ ጠፍተው ፡ እንዳያጠፉን ፡ እንጠንቀቅ ፡፡ በቀጣዩ ፡ ክፍል ፡ ደግሞ ፤ “ወንጌል ፡ በአሚን ፡ ብቻ ፡ ታድናለች” ፡ ትላላችሁ ፡ እያሉ ፡ የሚጃጃሉበትን ፡ ሉተራዊ ፡ አመለካከታቸውን ፡ በዝርዝር ፡ እንመለከታለሁ ፡፡ ምንም ፡ የማታውቁ ፡ ካሮች ፡ እባካችሁ ፡ ስለ ፡ አዛኝቱ ፡ ብላችሁ ፡ ስለማታውቁት ፡ ነገር ፡ አስተያየት ፡ አትስጡ ፡፡

No comments:

Post a Comment