በስመ
፡ አብ ፡ ወወልድ ፡ ወመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡
አሐዱ ፡ አምላክ
የሥሉስ
፡ ቅዱስ ፡ ህልውና
ዛሬ
፡ የምንመለከተው ፡ ሥላሴ ፡ በህልውና(በአነዋወር) ፡ አንዴት ፡ እንደሆኑና ፤ ቤተ ፡ አይሁድ ፡ ካሮች ፡ ሳይረዱት ፡ ሳያውቁት
፡ ብዙ ፡ ክርስቶሳውያንን ፡ ሁለተኛ ፡ እያጠመቅ ፡ አይሁድ ፡ አረሚ ፡ ለሚያደርጉበት ፡ የክሕደት ፡ ቃል ፡ ፍቱን ፡ መድኃኒት
፡ የሚሆን ፡ መልእክትን ፡ ይሆናል ፤ ይህንን ፡ ቃልም ፡ የጻፍኩላችሁ ፡ ቤተ ፡ አይሁድ ፡ ኬልቄዶናውያን ፡ እቤታቸው ፡ ታቅፈውት
፡ ከሚገኘው ፡ አክሲማሮስ ፡ ከተባለ ፡ የብራና ፡ መጽሐፋቸው ፡ ነው ፡፡ =============================================
የሥላሴ
፡ ህልውና ፡ እንዴት ፡ ነው ፡ እንደምን ፡ ይኖራሉ ፡ ቢሉ ፤ እንደ ፡ አንድ
፡ ሰው ፡ ይኖራሉ ፡፡ የ1ድ ፡ ሰው ፡ ኑሮው ፡ እንዴት ፡ ነው ፡ ቢሉ ፤ በልቡ ፡ አስቦ
፡ በቃሉ ፡ ተናግሮ ፡ በእስትንፋሱ ፡ ተንፍሶ ፡ ደኅና ፡ ሁኖ ፡ ይኖራል ፡፡ በልቡ ፡ ሲያስብ ፡ ቃሉና ፡ እስትንፋሱ ፡ አይለዩም ፤ በቃሉም ፡ ሲናገር ፡ ልቡናው ፡ እስትንፋሱ ፡ አይለዩም ፡፡ ሥላሴም ፡ እንዲህ ፡ ናቸው ፡፡ ሰው ፡ ቃሉ ፡ እስትንፋሱ ፡ ሳይለየው ፡ በልቡ ፡ አስቦ ፡ ደኅና ፡ ሁኖ ፡ እንዲኖር ፡ ወልድና ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስም ፡ ለባውያን ፡ በአብ ፡ ናቸው ፤ በአብ ፡ ያስባሉ ፤ ለወልድና ፡ ለመንፈስ
፡ ቅዱስ ፡ ልባቸው ፡ አብ ፡ ነው ፤
ሌላ ፡ ልብ ፡ የላቸውም ፡፡ ሥላሴ ፡ እምቅድመ
፡ ዓለም ፡ ያስቡ ፡ ነበር ፡ ማለት ፡ የማያውቁት ፡ ነገር ፡ ኑሮ ፡ አውጥተው ፡ አውርደው ፡ የሚናገሩ ፡ ሁነው ፡ አይደለም ፤ ነገር ፡ ግን ፡ ሥላሴ ፡ እምቅድመ ፡ ዓለም ፡ ሳሉ ፡ በዚህ ፡ ዓለም ፡ የሚሠራውን ፡ ሥራ ፡ የሚደረገውን ፡ ነገር ፡ ሰፍረው ፡ ቆጥረው ፡ ያውቁት ፡ ነበር ፡፡ ዛሬም ፡ ሥላሴን ፡ ያስባሉ ፡ ማለት ፡ ያንን ፡ እምቅድመ ፡ ዓለም ፡ የሚአውቁትን ፡ ነገር ፡ መዓትም ፡ ምሕረትም ፡ ቢሆን ፡ ይህን ፡ ጊዜ ፡ እንዲህ ፡ ይደረግ ፡ ብለው ፡ ጊዜ ፡ ይሰጡታልና ፡ ሥላሴ ፡ እምቅድመ ፡ ዓለም ፡ ያስቡ ፡ ነበር ፡ ማለት ፡ ስለዚህ ፡ ነው ፡፡ “ውእቱሰ ፡ እምቅድመ ፡ ይኩን ፡ አእመረ ፡ ወእምቅድመ ፡ ይግበር ፡ ፈጸመ(እርሱ ፡ ሳይደረግ ፡ አወቀ ፤ ሳይሰራ ፡ ፈጸመ)” ፡ እንዳሉ ፡ ቅዳሴ ፡ 300(t ፡ 38) ፤ አንድም ፡ “እምቅድመ ፡ ይፍጥሮ ፡ ለአዳም ፡ የአምር ፡ ግብሮ (አዳምን ፡ ሳይፈጥረው ፡ ሥራውን ፡ ያውቃል)” ፡ እንዳሉ ፡ ቅዳሴ ፡ 300(t ፡ 39) ፤ አንድም ፡ “ወለነዋህኒ ፡ እምርሑቅ
፡ የአምሮ() ፡ እንዳለ ፤ እግዚአብሔር ፡ መስተበቅል
፡ ገሀደ(እግዚአብሔር ፡ በግልጽ ፡ ተበቃይ ፡
ነው)” ፡ እንዳለ(መዝ ፡ 93 ፡ t ፡ 1) ፡፡
ሰው
፡ ልቡ ፡ እስንፋሱ ፡ ሳይለየው ፡ በቃሉ ፡ ተናግሮ ፡ ደኅና ፡ ሁኖ ፡ እንዲኖር ፡ አብና ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ነባብያን
፡ በወልድ ፡ ናቸው ፡፡ በወልድ ፡ ይናገራሉ ፡ ለአብና ፡ ለመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ቃላቸው ፡ ወልድ ፡ ነው ፤ ሌላ ፡ ቃል ፡
የላቸውም ፡፡ ሰው ፡ ልቡ ፡ ቃሉ ፡ ሳይለየው ፡ በእስትንፋሱ ፡ ተንፍሶ ፡ ደኅና ፡ ሁኖ ፡ እንዲኖር ፡ አብና ፡ ወልድም ፡
በመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ሕያዋን ፡ ሁነው ፡ ይኖራሉ ፡፡ ለአብና ፡ ለወልድ ፡ ሕይወታቸው ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ነው ፤ ሌላ ፡
ሕይወት ፡ የላቸውም ፡፡ “አብኒ ፡ ልቦሙ ፡ ለወልድ ፡ ወለመንፈስ ፡ ቅዱስ ፤ ወልድኒ ፡ ቃሎሙ ፡ ለአብ ፡ ወለመንፈስ ፡ ቅዱስ
፤ መንፈስ ፡ ቅዱስኒ ፡ ሕይወቶሙ ፡ ለአብ ፡ ወለወልድ(አብ ፡ ለወልድና ፡ ለመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ልባቸው ፡ ነው ፤ ወልድም
፡ ለአብና ፡ ለመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ቃላቸው ፡ ነው ፤ መንፈስ ፡ ቅዱስም ፡ ለአብና ፡ ለወልድ ፡ ሕይወታቸው ፡ ነው)” ፡ እንዳለ
፡ አቡሊዲስ ፡ ዘሮሜ(ሃይ.አበው ፡ ምዕ ፡ ፡ ክ ፡ 2
፡
t ፡ 8)
፡፡
በተዋሕዶ ፡ ከበረ ፡ የሚሉ
፡ ሰዎች ፡ ግን ፡ የእስትንፋስ ፡ ትርጓሜው ፡ ሕይወት ፡ እንደሆነ ፡ ባያውቁ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ለአብና ፡ ለወልድ ፡
እስትንፋሳቸው ፡ ነው ፡ እንጅ ፡ ሕይወታቸው ፡ አይደለም ፡ ብለው ፡ ተነሥተዋል ፡፡ እንዲህም ፡ ማለታቸው ፡ ሦስቱን ፡ ሕይወት
፡ ያልን ፡ እንደሆነ ፡ ነሥአ ፡ ተወክፈ ፡ ከማለት ፡ እንድናለን ፤ በተዋሕዶ ፡ ከበረ ፡ ለማለት ፡ ይመቸናል ፡ ብለው ፡
ነው ፡፡ ለነዚህ ፡ ምን ፡ ይመልሷል ፡ ቢሉ ፤ መላእክት ፡ በጥንተ ፡ ፍጥረቱ ፡ “መኑ ፡ አንተ” ፡ ብለው ፡ በጠየቁት ፡
ጊዜ ፡ እራሱ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ “አነ ፡ ውእቱ ፡ ሕይወቱ ፡ ለዘገብረ ፡ ሰማየ ፡ ወምድረ(እኔ ፡ ሰማይን ፡ እናንተንም
፡ ምድርንም ፡ ለፈጠረ ፡ ሕይወቱ ፡ ነኝ)” እንዳለ ፡ አክሲማሮስ ፡ ዘእሑድ(ክ ፡ 2 ፡ ቊ
፡ 5) ፡፡
ለራሱማ ፡ ቢሆን ፡ “ሕይወት ፡ ለርእስየ” ፡ ባለ ፡ ነበር ፡ እንጅ ፡ “ሕይወቱ ፡ ለዘገብረ ፡ ሰማየ ፡ ወምድረ” ፡ ባላለ
፡ ነበር ፤ ሰማይን ፡ ምድርን ፡ ለፈጠረ ፡ ለአብ ፡ ሕይወቱ ፡ ነኝ ፡ ሲል ፡ ነው ፡ እንጅ ፤ ሕይወትነቱን ፡ ሲያመለክት
፡ “ወበከመ ፡ ነፍስከ ፡ ለሥጋከ ፡ ሕይወት ፡ ከማሁ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስኒ ፡ ሕይወቶሙ ፡ ለአብ ፡ ወለወልድ(ነፍስ ፡ ለሥጋ
፡ ሕይወት ፡ እንደሆነችው ፡ እንዲሁ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስም ፡ ለአብና ፡ ለወልድ ፡ ሕይወታቸው ፡ ነው )” ፡ እንዳለ ፡ አረጋዊ
፡ መንፈሳዊ(ድር ፡ 22) ፡፡ እንዲህም ፡ ማለቱ ፡ ነፍስህ ፡ ለሥጋህ ፡ ሕይወት ፡
ሁናው ፡ እንዲኖር ፤ ለአብና ፡ ለወልድም ፡ ሕይወታቸው ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ነው ፡ ሌላ ፡ ሕይወት ፡ የላቸውም ፡ ሲል ፡
ነው ፡፡ “ነአምን ፡ ከመ ፡ አብ ፡ ልብ ፡ ወወልድ ፡ ንባብ ፡ ወመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ሕይወት(አብ ፡ ልብ ፡ እንደሆነ ፤ ወልድም
፡ ንግግር ፡ እንደሆነ ፤ መንፈስ ፡ ቅዱስም ፡ ሕይወት ፡ እንደሆነ ፡ እንመን)” ፡ እንዳለ ፡ ያዕቆብ ፡ ዘእልበራዳኢ(ምዕ
፡ 3 ፡ ቊ
፡ 13) ፤
አንድም ፡ “ንሕነሰ ፡ ክርስቶሳውያን ፡ ኢንብል ፡ በእንተ ፡ መለኮተ ፡ ቅድስት ፡ ሥላሴ ፡ አሐደ ፡ አካለ ፡ ወዘንተ ፡ ሶበ
፡ ንቤ ፡ ንትሜሰል ፡ ከመ ፡ አይሁድ ፡ እለ ፡ ይሰልብዎ ፡ ንባቦ ፡ ሕይወቶ(እኛ ፡ ክርስቶሳውያን ፡ ግን ፡ የቅድስት ፡
ሥላሴ ፡ ባሕርይ ፡ አንድ ፡ ነው ፡ ስለአልን ፡ አንድ ፡ አካል ፡ ነው ፡ አንልም ፤ ይህንን ፡ ብንናገርስ ፡ አምላክ ፡ ያላደረባቸውን
፡ ቃሉን ፡ ሕይወቱን ፡ ያሳጡተርን ፡ አይሁድን ፡ መምሰላችን ፡ ነው)” ፡ እንዳለ ፡ አባ ፡ ስኑትዩም ፡ ዘእለእስክንድርያ(ሃይ.አበው
፡ ምዕ ፡ 110 ፡ ክ
፡ 2 ፡ t ፡ 11) ፡
ብሏል ፡ ሲሏቸው ፡ በዚህ ፡ ይረታሉ ፡፡ ስለዚህም ፡ ነገር ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ለአብና ፡ ለወልድ ፡ እስትንፋሳቸው ፡ ነው
፡ እንጅ ፡ ሕይወታቸው ፡ አይደለም ፡ ማለት ፡ ክሕደት ፡ ነው ፡፡ ለአብና ፡ ለወልድ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ሕይወታቸው ፡
ነው ፡ ካሉ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ቢለያቸው ፡ መዋትያን ፡ መሆናቸው ፡ ነዋ ፡ ቢሉ ፤ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ለአብና ፡ ለወልድ
፡ የማይለይ ፡ የባሕርይ ፡ ሕይወታቸው ፡ ነውና ፡ መዋትያን ፡ አይደሉም ፡ “ወአልቦ ፡ ፍልጠት ፡ ማዕከለ ፡ ልቡናሁ ፡ ወንባቡ
፡ ወሕይወቱ(በሕይወቱ ፡ በንግግሩና ፡ በልቦናው ፡ መካከል ፡ ልዩነት ፡ የለም)” ፡ እንዳለ ፡ ያዕቆብ ፡ ዘእልበረዳኢ(ምዕ
፡ 3 ፡ ቊ
፡ 13) ፡፡
መንፈስ
፡ ቅዱስ ፡ ለአብና ፡ ለወልድ ፡ ሕይወታቸው ፡ ነው ፡ ካሉ ፤ “ወሕይወተ ፡ አብ ፡ ዘኢያስተርኢ(የማይገለጽ
፡ የአብ ፡ ሕይወት)” ፡ እንዳለ ፡ መጽሐፈ ፡ ኪዳን ፡ ወልድን ፡ ሕይወተ ፡ አብ ፡ ይለዋልሳ ፡ ይህ ፡ እንዴት
፡ ነው? ፡ ቢሉ ፤ ይህስ ፡ መዓዛ ፡ ዕጣን ፡ እንደማለት ፡ ነው፡፡ መዓዛ ፡ ዕጣን ፡ ማለት ፡ ከዕጣን ፡ የሚገኝ ፡ ሽታ
፡ ነው ፡ እንጅ ፡ ለእጣን ፡ የሚሸተው ፡ ሽታ ፡ ማለት ፡ አይደለም ፤ እንደዚህም ፡ ሁሉ ፡ ወልድ ፡ ለአብ ፡ ሕይወት ፡
ሆኖት ፡ አይደለም ፡፡ ነገር ፡ ግን ፡ አብ ፡ ወልድን ፡ ወርደህ ፡ ተወልደህ ፡ ተሰቅለህ ፡ ዓለምን ፡ አድን ፡ ብሎ ፡ አዝዞ
፡ ሰጥቷልና ፡ አብ ፡ የሰጠን ፡ ሕይወት ፡ ማለት ፡ ነው ፡ እንጅ ፡ ወልድ ፡ ለአብ ፡ ሕይወቱ ፡ ነው ፡ ማለት ፡ አይደለም
፡፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ለአብ ፡ ሕይወቱ ፡ ነው ፡ ካሉ ፡ ሕያው ፡ ያሠርፃል ፡ እንጅ ፡ ሙት ፡ ያሠርፃልን ፡ አብ ፡ በማን
፡ ሕያው ፡ ሁኖ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስን ፡ አሠረፀዋ!? ፡ ቢሉ ፤ በሥላሴ ፡ ሦስትነት ፡ መቀዳደም ፡ መከታተል ፡ ቢኖርባቸው ፡ ኖሮ ፡ አብ ፡ በማን ፡
ሕያው ፡ ሁኖ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስን ፡ አሠረፀ ፡ በተባለ ፡ ነበር ፤ ነገር ፡ ግን ፡ በZeሦስትነት
፡ መቀዳደም ፡ መከታተል ፡ የለባቸውምና ፡ አብ ፡ በመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ሕያው ፡ ሁኖ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስን ፡ አሠረፀው፡፡
መንፈስ
፡ ቅዱስ ፡ ለአብና ፡ ለወልድ ፡ ሕይወታቸው ፡ ብቻ ፡ አይደለም ፡ ክብራቸውም ፡ መንግሥታቸውም ፡ ነው፡፡ የዚህ ፡ ዓለም ፡
ንጉሥ ፡ በዘውድ ፡ እንዲነግሥ ፤ በወርቅ ፡ በብር ፡ እንዲከብር ፤ አብና ፡ ወልድም ፡ በመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ይነግሡበታል ፡
ይከብሩበታል ፡ ማለት ፡ አይደለም ፡፡ ነገር ፡ ግን ፡ የንጉሥ ፡ መንግሥቱ ፡ በሕይወቱ ፡ ሳለ ፡ እንጅ ፡ ከሞተ ፡ በኋላ
፡ ክብረት ፡ የለውም ፡ ከሞተስ ፡ በኋላ ፡ ስንኳን ፡ ክብረት ፡ ይኖረው ፡ ቀድሞ ፡ ሳለ ፡ በሕይወቱ ፡ በአዳራሽ ፡ በዙፋን
፡ በድንኳን ፡ ጃንሆይ ፡ ንጉሥ ፡ ሆይ ፡ እየተባለ ፡ ሲጋረድ ፡ ሲጓደድ ፡ ይኖር ፡ የነበረው ፡ ሰው ፤ ነፍሱ ፡ ከሥጋው
፡ ስትለይ ፡ ስመ ፡ መንግሥቱ ፡ አብሮ ፡ ተለይቶት ፡ አስከሬን ፡ እጠቡ ፡ አስከሬን ፡ አውጡ ፡ ይባላል ፡እንጅ ፡ ከሞተ
፡ በኋላ ፡ ስመ ፡ መንግሥቱን ፡ የሚአነሳው ፡ የለም ፡፡ እንደዚህም ፡ ሁሉ ፡ የአብና ፡ የወልድ ፡ መንግሥታቸው ፡ በመንፈስ
፡ ቅዱስ ፡ ሕያው ፡ ሁነው ፡ ነውና ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ለአብና ፡ ለወልድ ፡ መንግሥታቸው ፡ ነው ፡ ማለት ፡ ለዚህ ፡
ነው፡፡ “ወዓዲ ፡ ይስእልዎ ፡ ከመ ፡ ያምፅእ ፡ ሎሙ ፡ መንግሥቶ ፡ ዝ ፡ ውእቱ ፡ መንፈስ
፡ ቅዱስ()” ፡ እንዲል ፤ አንድም ፡ “ፍካሬ ፡ መንግሥቱሰ ፡ ሱታፌ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ውእቱ()” ፡ እንዳለ ፡ ትርጓሜ
፡ ወንጌል() ፡፡
መንፈስ
፡ ቅዱስ ፡ ለአብና ፡ ለወልድ ፡ ክብራቸው ፡ ነው ፡ ማለት ፤ የዚህ ፡ ዓለም ፡ ሰው ፡ በወርቅ ፡ እንዲከብር ፡ አብና ፡
ወልድ ፡ በመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ይከብሩበታል ፡ ማለት ፡ አይደለም ፤ የንጉሥ ፡ ክብረቱ ፡ መንግሥቱ ፡ ሳለ ፡ በሕይወቱ ፡ ነው
፡ እንጅ ፡ ከሞተ ፡ በኋላ ፡ ክብረት ፡ የለውም ፡፡ ከሞተስ ፡ በኋላ ፡ ስንኳን ፡ ክብረት ፡ ይኖረው ፡ ዘንድ ፡ ቀድሞ ፡
በሕይወቱ ፡ ሳለ ፡ በንብረት ፡ ከብሮ ፡ ገኖ ፡ ይኖር ፡ የነበረው ፡ ሰው ፤ ነፍሱ ፡ ከሥጋው ፡ ስትለየው ፡ ድሪውን ፡ ካንገቱ
፡ ልብሱን ፡ ከአካላቱ ፡ ገፈው ፡ በግማሽ ፡ ሰሌን ፡ በአሞሌ ፡ ነጠላ ፡ ገንዘው ፡ መቃብር ፡ ያወርዱታል ፡ እንጅ ፡ ያ
፡ ሁሉ ፡ ንብረቱ ፡ አብሮት ፡ አይቀበርም ፡፡ “ዕራቅየ ፡ ወጻዕኩ ፡ እምከርሠ ፡ እምየ ፡ ወዕራቅየ ፡ እገብዕ ፡ ውስተ ፡
መሬት(ከእናቴ ፡ ማኅፀን ፡ እራቁቴን ፡ ወጥቻለሁ ፤ እራቁቴንም ፡ ወደ ፡ ምድር ፡ እመለሳለሁ)” ፡ እንዳለ ፡ ኢዮብ(ምዕ ፡
1 ፡ t ፡ 11)
፤ እንደዚህም ፡ አብና ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡
ክብረታቸው ፡ መንግሥታቸው ፡ በመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ሕያው ፡ ሁነው ፡ ነውና ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ለአብና ፡ ለወልድ ፡ ክብራቸው
፡ ነው ፡ ማለት ፡ ስለዚህ ፡ ነው ፡፡ “ዘሰ ፡ ኢያጠሪ ፡ እምብዕለ ፡ ክርስቶስ ፡ ዝ
፡ ውእቱ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ነዳይ ፡ ውእቱ()” ፡ እንዳለ ፡ ስምዖን ፡ ዘአምድ() ፡፡
ምስጋና ፡ ለአንዱ ፡ አምላክ ፡ ለቅድስት ፡
ሥላሴ
ክብር ፡ ለአምላክ ፡ እናት ፡ ለድንግል ፡ ማርያም
ክብር ፡ ለመስቀለ ፡ ክርስቶስ ፡ እጸመድኃኒት
፡ ኃይልነ ፡ ወጸወንነ
ይህ ፡ ጽሁፍ ፡ ወልደ ፡ አብ ፡ ላይም ፡ ቁልጭ
፡ ብሎ ፡ አለ ፡ ቤተ ፡ አይሁድ ፡ አይናችሁን ፡ ከፍታችሁ ፡ ተመልከቱት ፡ ተሰናክላሁ ፡ አታሰናክሉ ፡ እባካችሁ
No comments:
Post a Comment