Thursday, June 4, 2020

“ዛቲመ ትርጓሜሃ ለቅብዓት እስመ መንፈስ ቅዱስ አንጽሐ ሥጋሁ ለአዳም”==ከፍል ሦስትት


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!
ዛቲመ ትርጓሜሃ ለቅብዓት እስመ መንፈስ ቅዱስ አንጽሐ ሥጋሁ ለአዳም”==ከፍል ሦስትት
===========================+====================
ይድረት “frehiwot aregie”

========+==========
1ኛ‹‹‹‹‹‹‹ “3 ንባብ ቅብዓ መንፈስ ቅዱስ ነው ያለው ሲተረጉም የመንፈስ ቅዱስ ቅብአት ተብሎ እንጅ ቅብአት ያለው መንፈስ ቅዱስ አይደለም” ›››››››››››››ብለሃል ፤ ወዳጃችን አክሲማሮስ እየነገረን ያለው “ወአንትሙሰ ቅብዓት ብክሙ እምነ መንፈስ ቅዱስ” እንዳለ ፤ ሕዝቡ አሕዛቡ የጸጋ ልጅነት የተወለድንበት እርሱ መድኅን ክርስቶስ በማኅፀነ እሙ ሰው ስለመሆኑ በሰውነቱ ልደት ባሕርያዊትን ከአብ የተወለደበት ቅብዓቱ መንፈስ ቅዱስ እደሆነ ነው ፡፡ “ይህ ቅብዓት ምንድን ነው ቢሉ መንፈስ ቅዱስ ነው” ብሎ እየነገረን ሳለ ልቡናን እንደፈርዖን ማደንደን አይጠቅምህም  ፡፡

2ኛ‹‹‹‹‹‹‹ “4
ለቅዱሳት መጻሕፍት ረቂቁን ነገር ለመንፈስ ቅዱስ መስጠት ልማድ ነው ።ወልህቀ በመንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ አደገ መንመንፈስ ቅዱስ አደረባት እያለ ረቂቁን የመይመረመር ነገር ሁሉ ለመንፈስ ቅዱስ ይሰጣልና ። ስለዚህ ቅብአት ነን ባዮች አስተውሉ”›››››››››››››ብለሃል ወዳጃችን እኛ አንተ ሳትነግረን ቅዱስ መጽሐፍ ረቂቁን ነገር ለመንፈስ ቅዱስ እየሰጠ እንዲናገር በደንብ እናውቀዋለን ፡፡ አስተውል ! መጻሕፍት ረቂቁን ነገር ለመንፈስ ቅዱስ መስጠታቸው እኛ ሰዎች ሥራችንን የምንሰራው በነፍሳችን ሕያዋን ሁነን እንደሆነ ሁሉ ሥላሴም ማንኛውንም ሥራቸውን ሲያከናውኑ በመንፈስ ቅዱስ ሕያው ሁነው ነውና ስለዚህ ነው ፡፡

“ዛቲመ ትርጓሜሃ ለቅብዓት እስመ መንፈስ ቅዱስ አንጽሐ ሥጋሁ ለአዳም”==ከፍል ሁለት


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!
ዛቲመ ትርጓሜሃ ለቅብዓት እስመ መንፈስ ቅዱስ አንጽሐ ሥጋሁ ለአዳም”==ከፍል ሁለት
===========================+====================
ይድረት “frehiwot aregie”
========+==========
1ኛ‹‹‹‹‹‹ “3ተኛ ተዋሐደ ተብሎ ይተረጎማል ።ቅብአቶች ከእኛ የሚለዩበት አንዱ ይህ ነው። የፈለገው ቢሆን ቀብአን ተዋሐደ ብለው አይተረጉሙም ግን መጽሐፍ እንዲህ ይላል፦አባ ጊወርጊስ በመጽሐፈ አርጋኖን ላይ እንዲህ ይላል ዘተቀባአከ ስጋሃ ለማርያም ይላል ።ይህ ንባብ የሚተረጎመው የማርያምን ስጋ የተዋሐድህ ተብሎ ነው። ከዚህ ውጭ የፈለገው ሊቂ ይምጣ ሊተረጉመው አይችልም”››››››››ብለሃል ፤ ከዚህ በፊት በክፍል አንድ እንደጻፍኩልህ ከቄርሎስና ከአፈወርቅ ትምህርት ጋር የማይገጥም ነውና በምንም ተዓምር ተቀብዐ ተዋሐደ ተብሎ አይተረጎምም ፡፡ የጠቀስካት የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የአርጋኖን መልእክት” ዘተቀባዕከ ሥጋሃ ለማርያም” የሚለው ቃል ትርጓሜው ሰም ለበስ ግስ ነውና ሰም ለበስ ትርጓሜ ይተረጎማል ፡፡ ይህም ማለት  አባ ጊዮርጊስ በአንቀጸ ተቀብዓ ተገብቶ ምሥጢር ስቦታልና ዘተቀባዕከ ሥጋሃ አለው ፤ ትርጓሜው ግን እዚያው አርጋኖን ላይ ቁልጭ ብሎ አለ ይህንን ከተናረ በኋላ “እስመ ክርስቶስ ብሂል ቅቡዕ በከመ ተርጎመ ቄርሎስ ሊቀ ጳጳሳት)” በማለት አስቀምጦታል ፡፡ ቅዱስ ቄርሎስ የተረጎመው ደግሞ “በእንተ ቅብዓት ተሰምየ ክርስቶስ እስመ ክርስቶስ ብሂል ቅቡዕ በመንፈስ ቅዱስ ብሂል” ብሎ ነው ፡፡በመሆኑም ይህች ዘተቀባዕከ ሥጋሃ ለማርያም የሚለው ቃል በሥጋ ማርያም የተቀባህ አንተነህ ማለቱ ነው ይህ የወርቅ አነጋገር ነው ፡፡

Wednesday, June 3, 2020

“ከዚህ የበለጠ ምሥጢር ምን ምሥጢር አለ????”= ክፍል አንድ



በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ!!!

“ከዚህ የበለጠ ምሥጢር ምን ምሥጢር አለ????”= ክፍል አንድ

“ለመኑ እመላእክቲሁ ይቤሎ እምአመ ኮነ ወልድየ አንተ ወአነ ዮም ወለድኩከ ፤ ወካዕበ አነ እከውኖ አባሁ ወውእቱ ይከውነኒ ወልድየ (ከሆነ ጀምሮ ከመላእክት ወገን “አንተ ልጄ ነህ እኔ ዛሬ ወለድኩህ፤ ዳግመኛም እኔ አባት እሆነዋለሁ እሱም ልጄ ይሆነኛል” ማንን አለው? ዕብ ምዕ 1 ቁ 5፡፡
==============+==================================
በክርስቶስ ክርስቲያን በወልድ ውሉደ እግዚአብሔር የተሰኛችሁ በሜሮን ቅብዓት የታተማችሁ ኦርቶዶክሳውያን ወንድም እህቶቼ እንደምን ሰነበታችሁልኝ! ፡፡ አምላክ በቸርነቱ ጠብቆ ለዚህ ስላደረሰን ክብርና ምሥጋና በፈጠረው ፍጥረት አንደበት ሁሉ ይድረሰው ፡፡ ለዛሬ የምንነጋገርበት ዋና ዓላማችን በዚህ በምሥራቃዊት ምድር ተወልደን አድገን ለከፍተኛ ዘመናዊ ትምህርት ወደ ዘመናዊ መካነ አእምሮ ቀያችንን ለቀን ስንጓዝ በክርስትና ሃይማኖታችን ከተለያዩ አካላት የሚቀርቡ ጥያቄዎች ልቡናችንን እያወኩ ፤ ወደ ሁለተኛ ጥምቀት እያመሩን ስለሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ስለምናምናት ክርስትናችን ምን ይላል የሚለውን እውነታ ለማስረዳት ያህል ነው ፡፡
እነሆም የማናውቅ ከሆነ ለማወቅ መዘጋጀት ፤ የምናውቅ ከሆነ ደግሞ ለሌሎች ለማሳወቅ መትጋት እዳለብን መዘንጋት የለብንም ፡፡ ስለሆነም መጽሐፍ ቅዱስ የተናገረውን እውነት ለምን እደዚህ ይሆናል ብለን እንጠይቅ ዘንድ ተገቢ አይደለም ፡፡ ለምሳሌ፡- መጽሐፍ ቅዱስ አብ ወልድን ቀባው አከበረው ይላል ፡፡ ታዲያ እዚህ ላይ ለምን ያከብረዋል? እዴት ሊሆን ይችላል? የሚሉ ጥያቄዎች ዋጋ የሌላቸው ጥያቄዎች ናቸው ፡፡ ምክንያቱም እኛ ፍጡራን ለምን ሊያከብረው ይችላል? የሚል ጥያቄን የመጠየቅ አቅም የሌለን የአከበረበት ምሥጢሩ ከኅሊናችን በላይ ስለሆነ ቅዱሱ መጽሐፍ አከበረው ካለው እኛም አከበረው የሚለውን እንቀበላለን እንጅ ፤ ካላገባን ገብተን ስለምን ሊያከብረው ይችላል እንዴት እንዲህ ሊሆን ይችላል? ብሎ ያዙኝ ልቀቁኝ ማለት የማያዋጣ ነው ፡፡ ለምን ብንል እኛ ሰው የሚል ስም ተሰጠን?ለምን ዛፍ የሚል ስም አልነበረንም?ለምን በሁለት እራችን ሄድን ስለምን ዓራት እር አልኖረንም?.....የመሳሰሉትን ጥያቄዎች ብንጠይቅ ለአእምሮአችን የከበዱ ለኅሊናችንም የረቀቁ ናቸው ፡፡ ታዲያ ይህንን ያልመለሰች ኅሊናችን ደፍራ ራሱ ባለቤቱ መድኅን ክርስቶስ “የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ላይ ነው ለድሆች ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛል” ብሎ የተናገረውን እውነታ “ለምን ሊቀባው ይችላል አልቀባውም፣ ምንም ቅብዓት አይፈልግም” እያሉ ቢፍጨረጨሩ ድንጋይ መንከስ ነው ፡፡ ምክንያቱም መድኅን ክርስቶስ በነቢዩ አድሮ ቀብቶኛል ብሎ ስለተናረ እኛ ቀብቶታል ብለን ማመን እንጅ አልቀባውም እንዳንልማ ራሱ እኮ ቀብቶኛል ብሎንናልና ውርደቱ ለማንም ሳይሆን ለራሳችን ነው ፡፡ ስለሆነም በመጽሐፍ ቅዱስ የምናምን ከሆነ ትክክለኛውን ትርጓሜ (ቀደምት አበው አጥርተው የተረጎሙትን) እየተረዳን በአቅማችንና በልካችን መኖር ይኖርብናል ፡፡

“ዛቲመ ትርጓሜሃ ለቅብዓት እስመ መንፈስ ቅዱስ አንጽሐ ሥጋሁ ለአዳም”==ከፍል አንድ


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!
ዛቲመ ትርጓሜሃ ለቅብዓት እስመ መንፈስ ቅዱስ አንጽሐ ሥጋሁ ለአዳም”==ከፍል አንድ
===========================+=================================
ይድረት ለ “frehiwot aregie”
========+==========
መምሕር እንደሆንክ በጽሁፍህ መጨረሻ ላይ ባስቀመጥከው መልኩ ልከህልናል ፡፡ መነሻ ሀሳብህም “ቅብአተ ማለት ምን ማለት ነው?” በሚል ጥያቄ ላይ ተመርኩዘህ ብዙ ነገር ዘላብደሃል ቀባጥረሃልም ፡፡ ቅብዓት ማለት ምን ማለት እንደሆነ በእኔ ገጽ ቅብዓት ማለት ምን ማለት ነው በሚል ርእስ ጽፌልሃለሁና ያንን ገብተህ ተመልከትልኝ እያልኩ በዚህ ዓምድ ስር ወዳጅህ “Hailemariam Mengstie” የተባለ ግለሰብ አሰባስቦ በአንድ ላይ ለለቀቀው ፈጠራችሁ መልስን መስጠት እጀምራለሁ ፡፡ የምጀምረውም “ዛቲመ ትርጓሜሃ ለቅብዓት እስመ መንፈስ ቅዱስ አንጽሐ ሥጋሁ ለአዳም” በሚለው የማቴዎስ ወንጌል አንድምታ ይሆናል ፡፡
1ኛ‹‹‹‹‹‹ “ይህ ቃል ብዙ ሰዎች እንደፈለጉት ይተረጉሙታል ።በተለይ ቅብአት ነን ብለው ስለ ቅብአት የሚከራከሩ ፣የሚጽፉ ያለ ትርጉም ትርጉም፣ ያለ ፍችው ፍች ፣ያለ ምስጢሩ ምስጢር ተሰጥቶት እናያለን”››››ብለህ ጽፈሃል ፤ በአምላክ ቸርነት ልለምንህና የት ላይ ያለ ፍችው ፍች ያለ ምሥጢሩ ምሥጢር እደሰጠነው ልትጽፍልኝ ይቻልህ ይሆን? ይህች በስማ በለው እየተውተረተረች የምትነገረዋ ከንቱ ለፈፋችሁ ሊያበቃላት ጫፍ ላይ ደርሳለች ፡፡
2ኛ‹‹‹‹‹‹ “በእኛ ቤትም ቀብአ ወይም ቅብአት የሚል ገጸ ንባብ ሲያገኙ ይህ የቅብአቶች ነው እያሉ ያለ መልሱ መልስ የሚሰጡን እንሰማለን”›››››››ይህ ሀሳብ አንተን ጨምሮ ይመለከትሃልና ስሕተት መሆናችሁን በደንብ መረዳት አለብህ፡፡
3ኛ‹‹‹‹‹‹“ቅብአትን ቅብአት ነን ባዮች ሲተረጉሙ እንዲህ ይላሉ፦
1
ቀብአ ማለት ቀባ ፣ለከከ፣ለቀለቀ፣ማለት ነው ፤ 2 ቀብአ ማለት አከበረ ማለት ነው ይሉና ከዚህ ውጭ ግን ቀብአን ተዋሐደ እያሉ ያለ ቋንቋው ያለ አገባቡ ያለ ስልቱ መተርጎም ስህተት ነው ብለው ተቀብአን ተዋሐደ ብሎ መተርጎም እንደማይገባ ይናገራሉ”››››››››ብለሃል ፤ በነገራችን ላይ ቀብዓን ቀብዓ ለከከ ለቀለከ ብለው የተረጎሙት ኢትዮጵያውያን የልሳነ ግእዝ ሊቃውንት ናቸው እንጅ እኛ የተረጎምነው አይደለንም ፡፡ ለአብነትም የቀለም ቀንድ አለቃ ኪዳነ ወልድ ቅብዓት ማለትን “መቅባት መቀባት አቀባብ ቅብነት ቅባት” ይሉታል ፤ ቀቢዕ የሚለውን ደግሞ መቅባት መቀባት መላከክ መለቅለቅ መሾም ለማክበር ለመፈወስ” ብለው ያብራሩታል (ገጽ 779-80) ፤ ሌላው ሊቅ ደስታ ተክለ ወልድም እንዲሁ “ቀባ(ቀብዐ) ላከከ ለቀለቀ ደለሰ(ቅቤን) ፡፡ የሕጻንን ሕዋሳት ሜሮን አስነካ ፤ በራስ ላይ ዘይት አፈሰሰ ፤ አከበረ ሾመ ሥልጣን ሀብት ሰጠ ችሎት አሳደረ ዐደለ ሰጠ ካህን ነቢይ ንጉሥ አደረገ” ብለው ትርጉመውታል (ዐዲስ ያማርኛ መዝገበ ቃላት ደስ ተክለወልድ) ፡፡ አስተውል እንግዲህ ይህንን ቀብዓ ወይም አከበረ የሚለው ቃል እንዴት እንደሚተረጎም ከሰዋስው ምሁራን መረጃ ከጠቀስን ቀብዐን ተዋሐደ ብሎ መተርጎም ጽኑዕ ክሕደት መሆኑን አጥብቀን እንናገራለን ፡፡ “ተቀብዓን ተዋሐደ” ብላችሁ ሰሙን ወርቅ አድርጋችሁ ያለ አገባቡ ብትተረጉሙት በክሕደት አረንቋ ውስጥ የሚዘፍቃችሁ ነው የሚሆነው ፡፡ ምክንያቱም ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳ 3 ላይ “መለኮቱሰ ኢይትቀባዕ(መለኮቱ ቅብዓትን አይሻም)” ይላልና ቅብዓት የሚለው ተዋሕዶ ተብሎ ተለውጦ ቢተረጎም “መለኮት አልተዋሐደም ተዋሕዶን አይሻም)” የሚል ክሕደትን ያሽክማችኋል ፡፡ ቅዱስ ቄርሎስም ድር 29 ላይ “ኢይጽሕቅ ቅብዓተ በህላዌሁ(በባሕርየ መለኮቱ ቅብዓትን አይሻም)” ብሏልና ቅብዓትን ያለ ምሥጢሩ ለውጦ ተዋሕዶ ቢሉት “በባሕርየ መለኮቱ ተዋሕዶን አይሻም)” ያሰኛልና ጽኑዕ ክሕደትን ያመጣል ፡፡ በመሆኑም ቅብዓት ክብር ተብሎ ሲተረጎም ተዋሕዶ ማለት ደግሞ አንድነት ተብሎ ይተረጎማል እንጅ ገልብጦ ቢተረጉሙት ገልብጦ ነው የሚጥል ፡፡

ቅብዓት ማለት ምን ማለት ነው? ክፍል አንድ


በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ!!!
++++++=+++++++++
ቅብዓት ማለት ምን ማለት ነው? ክፍል አንድ
==========+==========
ውድ መሢሐውያን (በተለምዶ በአለአዋቂቀው አነጋገር ቅብዓቶች የሚሏችሁ) እናት አባቶቼ ፤ ወንድም እህቶቼ እንደምን አላችሁልኝ ! በዚህ ጽሁፍ ቅብዓት ማለት ምን ማለት እንደሆነ በሰፊው ከቅዱስ መጽሐፍ ማስረጃ እየጠቀስን እያጣቀስን እንነጋገራለን ፡፡ በኦርቶዶክሳዊት ቅድስት ቤተክርሥቲያን ውስጥ ቅብዓት እና ተዋሕዶ ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል በተለየ ከዊኑ ቃል በመባል የሚታወቀው ፣ በተለየ ግብሩ ተወላዲ የሆነ አምላክ ወልደ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው በመሆኑ የፈጸማቸው ዓበይት ምሥጢራት ናቸው ፡፡ እነዚህንም ደጋግ አባቶቻችን አስተምረውናል ፡፡ እንደምን አስተምረውናል ቢሉ ቅዱስ አውሳብዮስ በድርሳኑ መንክረ ገብረ ወልደ እግዚአብሔር ስተ ከርሠ እሙ (የእግዚአብሔር ልጅ በእናቱ ማኅጸን ድንቅ ሥራን ሠራ) ፤ እስመ ፈጸመ ሥርዓተ ተዋሕዶ ወቅብዓት ምዕረ ከመ ቅጽበተ ዓይን (የቅብዓትና የተዋሕዶን ምሥጢር (ሥርዓት) እንደ ዓይን ጥቅሻ አንድ ጊዜ ፈጽሞአልና)” በማለት ይገልጣል ፡፡ ሌሎቹ የሐዲስ ኪዳ መምሕራን ደግሞ በማቴዎስ ወንጌል አንድምታ ምዕራፍ 1 ቁ 16 ላይ ሲዋሐድም ሲቀባም አንድ ጊዜ ነው ከመ ቅጽበተ ዓይን እለሰ የአምኑ ርቱዓ ይሜህሩ ከመ ተቀብዓ ቃል በሥጋሁ ፤ ወእምአመ ኮነ ቃል ሥጋ አሜሃ አስተርአየ በመንፈስ ቅዱስ” ብለው አስተምረውናል ፡፡ ዮሐንስ አፈወርቅም “ወእመ አኮ ቀዲሙ ዘወረደ ወእምዝ ተሠይመ (ቀድሞ ሰው እንዳልሆነ ኋላ እንዳልተሾመ መጠን አንድ ጊዜ ሰው ለመሆን እንደመጣ አስረዳ ፡፡ አንድም ቀድሞ ሰው እንዳልሆነ ኋላ እንዳልተሾመ አስረዳ ፡፡ ሰው ሁኖ ኑሮ ኑሮ ተቀባ የሚሉ አሉና እንዲህ አለ ፡፡ አንድም በተዋሐደ ጊዜ ተቀባ አለ)” (ድርሳን 15 105) ብሏል ፡፡ እንግዲህ በደንብ አስተውል ቅብዓትና ተዋሕዶ አንድ ጊዜ የተፈጸሙ ምሥጢራት መሆናቸውን እንረዳለን ፡፡