Friday, November 30, 2018

ይድረስ:- በስምህ መጠራት ላፈርከው “ጎጃም ደብረ ማርቆስ” ተብለህ በሀገር ስም ለተሰየምከው ግለሰብ


ብሂል ፩............................ "በእዉነት ማሕበረ ቅዱሳን ማህበረ ሰይጣን ነዉን? " አዎ ነው:: ለምን ቢባል የተወሰነውን ግብሩን በሁለት ክፍል አድርጌ “ስም ሰጥተው ግብር ነሱት” በሚል ርዕስ ስለለጠፍኩልህ ደግመህ ሁለቱንም ክፍል ገለልተኛ ሆነህ አንብበውና ትረዳዋለህ::
ብሂል ፪............................ “ለመሆኑ ይህንን ሁሉ የፍልስፍና ወሬህን ትናገር ዘንድ ምን አነሳሳህ?”............... እንዲህ እናገር ዘንድ የገፋፋኝማ:-
ሀ/ ድርጅቱ[ማቅ] በክርስቶስ ደም የተመሰረተችዋ ኩላዊት የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን በዘር፣ በቀለም፣ በጎሳ ከፍሎ የዘረኝነትን መርዝ ሲዘራ በማየቴ፣
ለ/ እናቱንና አባቱን የማያከብር ጎረምሳ ሕግ እየጣሰ፣ ሥርዓት እያፋለሰ፣ ሃይማኖት እያጣረሰ፣ ውሸት እያናፈሰ በማየቴ፣ 
ሐ/ ከውሻ ጋር ታግለው ቁራሽ ለምነው ፊደል ቆጠረው ከዲቁና እስከ ጵጵስና የደረሱትን የቤተ ክርስቲያን እንቁ ልጆች ቦታ በመንጠቅ ሳምንት፣ ሁለት ሳምንት በመመላለስ ሁሉን አወቅሁ፣ ሁሉን ደረስኩ በማለት የድርጅቱ አባላት የማይገባቸውን ቦታ ሲይዙ በማየቴ፣ 
መ/ የቤተ ክርስቲያንን ልዕልና በመዳፈርና ሙዳዬ ምጽዋቷ ባዶ ሲቀር በማየቴ፣
ሠ/ የማይደገሙ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያንን እንዲደገሙ ሲያደርግ በማየቴ፣ ዲያቆናትን፣ ካህናትን፣ ጳጳሳትን ሲያሳድድ በማየቴና ከዚህም በላይ መጥፎ መጥፎ ስራዎቹን በማየቴ ከክፉ ሥራው ይመለስ ዘንድ ባለማወቅም የድርጅቱ ተባባሪ የሚሆኑ ምዕመናንም መጥፉ ሥራውን ይረዱት ዘንድ በማህበራዊ ድረ ገጽ ለመልቀቅ ወሰንኩኝ::

Thursday, November 29, 2018

ይድረስ ለአከማቸዉ ደሴ( በዲማ ስሙ አብርሃም ደሴ )

 “ብርሃኑ ሻምበል ፀረ ወልድ ቅብዕ በተዋሕዶ ከበረ እንጅ ፀረ ተዋሕዶ አይደለም”  ክፍል- ዐራት

“ነጭ ዉሸትህን የምንፍቅናህ መደበቂያ አታድረገዉ”›››››››ብለህ ለለጠፍካት የሙት መንፈስ ለሚስተዋልባት የክሕደት ሀሳብ ማክሰሚያ ፡፡
ብሂል አንድ
=====================================================
ምስራቅ ጎጃም ውስጥ ከዲማ ውጭ ሌላ ቦታ ሂዳችሁ ተክሊል እንዳትፈፅሙ ያለው እሱ ነዉይህን ካለ ትክክል ነው። ምክንያቱም እውቱን ማሳየት የሃይማኖታችን ግዴታ ነው “›››››››››››ብለሃል ወዳጄ አከማቸዉ ደሴ !!!!!!! መጻሕፍት ፡ በአንደበታቸዉ ፡ የሚሰማቸዉ አጥተዉ ዘወትር የሞጮሁት ጩኸት ቢኖር “ወመኑ ፡ ሐሳዊ ዉእቱ ዘእንበለ ዘይክሕድ ወይብል ከመ ኢየሱስ ኢኮነ መሢሐ( ኢየሱስ መሢሕ አይደለም ብሎ ከሚክድ በስተቀር፤ የሚክድ ነዉ እንጅ ሐሰተኛ ማን አለ?” 1ኛ ፡ ዮሐ 2፡22 ላይ የተጻፈዉና

Wednesday, November 28, 2018

"ስም ሰጥተው ግብር ነሱት"


ክፍል [ 2/2 ]

የድርጅቱ ተልእኮ:- “ማኅበሩ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ውጤት የሆኑትን የተለያዩ ትምህርተ ሃይማኖት ማስፋፊያ ዘዴዎችን በመጠቀም ግቢ ጉባኤያትና ምእመናን የወንጌልን ትምህርት፣ ሥርዓት፣ ትውፊት፣ እንዲያቆዩና እንዲጠበቁ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር እንዲጠናከር አቅሙ እንዲያድግ ማድረግና በየዘመኑ የሚከሰቱ ተለዋዋጭ ሃይማኖታዊ፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ችግሮች በመቃኘት የቤተ ክርስቲያኒቱን ሐዋርያዊ አገልግሎት ማጠናከር፡፡” ይላል::

"ስም ሰጥተው ግብር ነሱት"

ክፍል [1/2]

የድርጅቱ ስያሜ:- “ማኅበረ ቅዱሳን እግዚአብሔር ያከበራቸው የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት በአጠቃላይ የቅዱሳን ገድል፣ ትሩፋትና አማላጅነት የሚዘከርበት በመሆኑ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን›› የሚል ስያሜውን አግኝቷል፡፡” ይላል::
 ስያሜው ድንቅ ነው ዳሩ ግን ስም ሰጥቶ ግብር መንሳት ሆነ:: ለምን ቢባል ድርጅቱ የነቢያትን፣ የሐዋርያትን፣ የጻድቃንና የሰማዕታትን ተዓምር፣ ገድልና ትሩፋት ለማስመሰል[በማንኪያ] ይዘክርና ስውር አላማውን ሲያራምድ ይውላል:: ለመሆኑ የቅዱሳን አበው ግብራቸው ምንድን ነበር?
ቅዱሳን አበው [ነቢያት፣ ሐዋርያት፣ ጻድቃን፣ ሰማዕታት፣ ደናግል መነኮሳትና ሌሎችም የክርስቶስ ቤተሰቦች] የሚከተለውን ሲያደርጉ:-

Tuesday, November 20, 2018

“እንዘቦ በክሕደት ያወግዙ ካልአ--እነሱ በክሕደት ሳሉ ሌላዉን ያወግዛሉ”



በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ
እንዘቦ በክሕደት ያወግዙ ካልአ--እነሱ በክሕደት ሳሉ ሌላዉን ያወግዛሉ
=============================================================
የዛሬዋ መልእት የምታተኩረዉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ  ቤተክርስቲያን የበላይ ጠባቂ ቅዱስ ሲኖዶስና የዉግዘት ሥርዓቱ  ላይና የሚናገሩትን በማያዉቁ ቤተ አይሁድ ካሮች ላይ ይሆናል ፡፡ በዚህ ላይ አንተ ምን አገባህ ሲኖዶሱን የምትከስ የምትወቅስ ሌላም ሌላም ሀሳቦችን የምታንሸራሽሩ ሰዎች አትታጡም፡፡ ይሁን እንጅ የምንነጋገርበት ጉዳይ የሃይማኖት ልዕልና እንጅ የሲኖዶስ ልዕልና እስካልሆነ ድረስ አስፈላጊዉን ግብዓት የማስቀመጥ ክርስቲያናዊ ግዴታችን ነዉና የበኩሌን እል ዘንድ እሻለሁ ፡፡ የኢትዮጵያችን ሲኖዶሰ ክርስትና ከተወሰኑ አሠርት አመታት ወዲህ ልዕልናዉ አስቸጋሪና አዳጋች ሁኔታ ላይ እየወደቀ መሆኑን እየታዘብነዉ እንጀኛለን ፡፡ 1980ዎቹ መግቢያ ላይ በከባድ መንግስታዊ ፈተና እና ጭቆና ዐራተኛዉን በትረ ያሬክ በግፍ አባረዉበት ራቁቱን የቆየ ከዚያም ነፍሰ ኄር አባ ጳዉሎስ የተረከቡበት ዘመንን አሳልፏል ፡፡ አሁን በሕይወት  ያሉት አባ መርቆርዮስ ሀገራቸዉን ለቀዉ ከወጡ በኋላ ሲኖዶሱ በአንድ የሆነ ማኅበር የሚመራ እስከሚመስል ድረስ ዝብርቅርቁ ወጥቶ እስከ አሁኗ ድረስ የወረደ ሥራ እየተሠራ ይገኛል ፡፡ ባሳለፍነዉ 2010 ዓ.ም የመጽሐፉን ማንነት እኳን በደንብ አድርጎ ሳያይ በተለይ የሲኖዶሱ

Monday, November 5, 2018

“ሃይማኖት መሢሐዊት” ክፍል ሁለት


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ!!!
ይድረስ ምኑንም ሳትረዳዉ ከአባ ስምዓኮነ እና ከዓባይነህ ካሴ ገልብጠህ ለጠየቅኸኝ “Habtamu St” ለሚሉህ ግለሰብ
በአስተያየት መልክ ለሰጠኸኝ ጥያቄ መልስ
ሃይማኖት መሢሐዊትክፍል ሁለት

======================
ሌላ ዝርዝር ሐተታ ሳልገባ በቀጥታ ወደ ጥያቄዎችህ መልስ አመራለሁ ፡፡
1‹‹‹‹‹‹‹‹‹‹ “እንደው ሲጀመር ታድሶ፣ፔጤ(ቅባት)ቻሱን ሰጠን ልንከራከር አንችልም።ምክነያቱም ሌሎች ከተዋህደ ውጭ ክርስተያን አይባሉም”›››››››››››››››› ብለሃል ይህ የድኩማን ሀሳብ ነዉ ፡፡ ምክንያቱም ክርስቲያን የተሰኘነዉ በክርስቶስ ተቀብዖ ስለመሆኑ መጽሐፈ ምሥጢር እንዲህ ይለናልእኛ ግን ከእግዚአብሔር ቤተክርስቲያን አፀድ የሚያወጡንን መምህራን አንሻም በስማቸዉ ልንጠራ አንፈቅድም መምህራችን ክርስቶስ መምህራችሁ አንድ ክርስቶስ ነዉና ለራሳችሁ መምህራንን አትሰይሙ ብሎናልና።ስለዚህም እኛ ክርስቶስ እንደተባለ ክርስቲያን መሲሕ እንደተባለ መሲሐውያን ናዝራዊ እንደተባለ ናዝራውያን እንባላለን።የእኒህ የሦስቱ አጠራር ትርጓሜአቸዉ በአንድነት የተቀባ የተቀቡ ተብሎ ይተረጎማልናመጽሐፈ ምሥጢር 2049 ፡፡ ስለዚህ ቅቡዓን እኛ ክርስቶሳዉያን እንደምንባል መጽሐፍ ቅዱስ ይገርልናል ፡፡ እስኪ አንተ ንገረንተዋሕዶዎችብሎ ክርስቲያኖች የሚል ምን ማስረጃ ???????
2‹‹‹‹‹‹‹‹‹‹‹‹ “መተቸት ትችላለህ እንጂ መቼም አንድ አይደለንም ። እንደማንገናኝም ይሄው እየቃዠህ ነው”›››››››ብለሃል ወዳጄ ትችት ብቻ ሳይሆን ቃለ ግዘት ሁሉ እነግርሃለሁወመኑ ሐሳዊ ዘእንበለ ዘይክሕድ ወይብል ከመ ኢየሱስ ኢኮነ መሢሐ--ኢየሱስ መሢሕ አይደለም ብሎ ከሚክድ በቀር ሀሰተኛ ማን አለ” 1 ዮሐ 222
3‹‹‹‹‹‹‹‹‹‹ “የሚስጥረ ስላሴን ይንድብናል የህልውና መገናዘብን ያፍልስብናል።”››››››››››››ብለሃል በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ምሥጢረ ሥላሴን ያጸናል እንጅ አይንድም ስላሴ በአብ ልብነት ያስባሉ በወልድ ቃልነት ይናገራሉ በመንፈስ ቅዱስ ሕይወትነት ሕያዋን ሁነው ይኖራሉ፡፡ በመንፈስ ቅዱስ ከበረ ማለት በመንፈስ ቅዱስ ሕያው ሆነ ማለት ነው:: ዮሐ :፳፮-፳፯:: በህልውናም አብ ልብ ወልድ ቃል መንፈስ ቅዱስ ሕይወት ናቸው፡፡በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ ከበረ ማለትም በመንፈስ ቅዱስ ሕይወትነት ሕያው ሆነ ማለት ስለሆነ ህልውና አይፈርስም ይፀናል እንጅ፡፡