Sunday, January 20, 2019

“ሲያምኑ ግማሽ ሲተረጉሙ ዳሽ” ክፍል ሦስት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ
ሲያምኑ ግማሽ ሲተረጉሙ ዳሽክፍል ሦስት
ይድረስ “Habtamu St”››››››ለሚሉህ ግለሰብ በአስተያየት መስጫ ሳጥን ላይ ለጻፍክልኝ ጥያቄ መልስ
======================================
1‹‹‹‹‹‹ፊቴ እንዲያበራ እናቴ የቀባችኝ ቅባት፣
ካደረገኝ አምላክ ዘበምድር ወዘበሰማያት፣
የቅቤ መገኛ ላማችን እርሷም ድንቅ አምላክ ናት”›››››››››
ብለህ ለተናርካት ንግግርህ መልሴን በስንኝ ቋጠሮ
አስልተው ካልሰጡት ማረሚያና አራሚ
ንፍጥ ይለቀልቃል አላዋቂ ሳሚ፡፡
እንዳሉን አባቶች በሥነ ቃላቸው፤
ሰምተኸው ለማታውቅ ለአንተ ለእንግዳው፡
ጣዕመ ምሥጢሩ የቅብዓት ምሳሌው
መስሎ ይታይሃል ቅቤ ምናምኑ የላም የፍየሉ የግመል የአህያው፡፡
ዳሩ ግን ወዲህ ነው ድንቅ ንግግሩ፡
የተቀብዐ ዳገት ናሙና ምሥጢሩ፡፡
የሥላሴ ሕይወት መንፈሰ ቅግዚአብሔር፡
በላሞቹ ዉጤት በቅቤ በከንቱው
የሚለካ አይደለም አምላክ ዘለዓለም ነው፡፡
በትምርት ታጥቦ ዓይንን ካልገለጡ፤
ወደ መምህርነት ምንም ቢያንጋጥጡ
የተቀብዐ ዳገት የተሰብአ መውጫ፤
ከቶ አይገኝም በትዕቢት በአፍ ብልጫ፡፡
ብየሀለሁ፡፡

 “ሲያምኑ ግማሽ ሲተረጉሙ ዳሽ” ክፍል ሁለት፡፡

                                                  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ
 “ሲያምኑ ግማሽ ሲተረጉሙ ዳሽክፍል ሁለት፡፡
ይድረስ “Habtamu St”››››››ለሚሉህ ግለሰብ በአስተያየት መስጫ ሳጥን ላይ ለጻፍክልኝ ጥያቄ መልስ
======================================
መናገር ስለምንችል ብቻ ባንናገር መልካም ነው፤እኛ ተበላሽተን ሰውም እያበላሸን ነው”›››››››ብለሃል አዎ ወንድሜ ተበላሽታችሁ ትውልዱን አታበላሹት ነው የእኔም መልእክቴ
1‹‹‹‹‹‹‹‹ “በቅባት ነገሰ ማለት እየሱስን የባህሪ አምላክ ያሰኘዋል?”››››››”ዘአንገሦ ለሥጋ አዳም በመንፈስ ቅዱስ ወረሰዮ ቅዱሰ ወማኅየዌ--የአዳምን ባሕርይ በመንፈስ ቅዱስ ሕይወትነት ያከበረው የባሕርይ አምላክም ያደረገው እሱ ነው.አበው ዘእልሥጦ አግአያ 25
2‹‹‹‹‹‹‹‹ “.የባህሪ አምላክነትን እያነሳህ ሁለተኛ ከአብ ተቀበለ ማለት ፍጡርነትን አያሳይም?ሶስት ልደት አለዴ?አብ ሁለቴ ወለደው?ስላሴ ዘጠኝ ይሆናል እዴ?”›››››››››››ወንድሜ የባሕርይ አምክ መሆኑን የምታን ከሆነ የባሕርይ አምላክ ሰው ሁኖ የሰውነትን ገንዘብ(መቀበልን) በተዋሕዶ ገንዘቡ በማድረጉ  በሰውነቱ ተቀበለወበከመ ለአብ ቦቱ ሕይወት ኀቤሁ ከማ ለወልድኒ ወሀቦ ሕይከወት ከመ ይኩን ሕይወት ኀቤሁ--ለአብ በራሱ ሕይወት እዳው እንዲሁ ለወልድም ሕይወት ይኖረው ዘንድ ሕይወት ዘጠው….እስመ ወልደ እግዚአብሔር ኮነ ወልደ እጓለእመሕያውዮሐ 5 26-27 ብሎ ተናገረለት፡፡ ለምን ተቀበለ ብትለኝ ተወካፊነትን በተዋሕዶ ከሥጋ ስለተቀበለ ብየ እመልስሀለሁ፡፡ ስለዚህ ተወካፊነቱ በሰውነቱነ ነውና የባሕርይ አምላክነቱን የሚያጠፋበት አይደለም፡፡ ይህንንም ከሞቱ ጋር አስተባረህ ተመልተው፤ የማይሞት አምላክ መዋቲ ሥጋን ተዋሕዶ መዋቲነትን በተዋሕዶ ገንዘቡ በማድረጉ ሞተ በሥጋ ተባለለት ፡፡ ተቀበለ መባሉም እንዲሁ ነው፡፡ ሁለተኛ እያልክ ያልተጻፈ የምታነበውን ጉዞህን አስተካክል፡፡ ሁለተኛ አይደለም አንድ ጊዜ እንጅ ፡፡ ተቀበለ መባሉም በሥጋው ነው፡፡ ሁለተኛ እያልክ ስትቆጥር መጀመሪያ በመለኮት ዘንድ መስጠትና መቀበል አለበትን?ክርስቶስ ሞተ በሥጋ ማለት ፍጡርነትን ያሳያልን?ሦስት ልደት ላልካት ደግሞ ሦስት ልደት የለም፡፡አብ ሁለቴ ሳይሆን እድ ጊዜ ነው የወለደው፡፡ በተዋሕዶ ከበረ(ለሊሁ ቀባዒ ወተቀባዒ ወለሊሁ ቅብዕ ካችሁት) መለኮት ሦስ አካለ ስላሴን ዘጠኝ ማድረግ ነው፡፡

Saturday, January 12, 2019

ሲያምኑ ፡ ግማሽ ፡ ሲተረጉሙ ፡ ዳሽ


በስመ ፡ አብ ፡ ወወልድ ፡ ወመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ አሐዱ ፡ አምላክ ሲያምኑ ፡ ግማሽ ፡ ሲተረጉሙ ፡ ዳሽ ፡ ይህች ፡ ብሂል ፡ “የነሲብ ፡ ትርጓሜ” ፡ ብለን ፡ እንመለከታለን ፡፡

===============================================
በኢትዮጵያ ፡ ኦርዶክሳዊት ፡ ቤተክርስቲያን ፡ ውስጥ ፡ የሚገኙ ፡ “በተዋሕዶ ፡ ከበረ ፡ ወልድ ፡ ቅብዕ” ፡ ብለው ፡ የሚያምኑ ፡ ልዮናውያን ፤ የወልደ ፡ እግዚአብሔርን ፡ አምላክነት ፡ እናምናለን ፤ ተዋሕዶንም ፡ እንከተላን ፣ ይባስ ፡ ብሎም ፡ ስማችን ፡ ተዋሕዶ ፡ ነው ፡ ሲሉ ፡ ይደመጣሉ ፡፡ እነኝህ ፡ ሰዎች ፡ ተዋሕዶን ፡ እናምናለን ፡ እያሉ ፡ በተዋሕዶ ፡ ከበረ ፡ ወልድ ፡ ቅብዕ ፡ ማለትን ፡ ዘንቀው ፡ ቀላቅለው ፡ ያስተምራሉ ፡ ይደናበራሉም፡፡ ያም ፡ ሆነ ፡ ይህ ፡ ተዋሕዶና ፡ በተዋሕዶ ፡ ከበረ ፡ በመጻሕት ፡ ምሥጢርም ፡ ይሁን ፡ በቋንቋ ፡ ሕግ ፡ አንድ ፡ አይደሉም ፡ ልዩነታቸውም ፡ የሰማይና ፡ የምድር ፡ ያህል ፡ ነው፡፡