ወልደ ፡ አብ ፡ በወልደ ፡ አብ : ክፍል ፡ ሁለት
==================================
የጌታችን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅነት ፡ እና
የቤተ ፡ አይሁድ ፡
ካሮች ፡ ውድቀት
======================================
በገዛ
፡ ሥልጣኔ ፡ ተነሣሁ ፡ ሲል ፡ ለወልድ ፡ ከአብ ፡ ከመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ የተለየ ፡ ሥልጣን ፡ አለውና ፡ በተለየ ፡ ሥልጣኔ
፡ ተነሣሁ ፡ ሲል ፡ ነውን? ፡ ቢሉ ፤ ከአብ ፡ ከመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ጋር ፡ በሥልጣን ፡ ዕሪናውን ፡ ሲያጠይቅ ፡ እጅ ፡
የተነሣስ ፡ በ3ቱም ፡ ሥልጣን ፡ ነው ፡፡ “አማን ፡ በአማን ፡ ተንሥአ ፡ እሙታን ፡ በኃይለ ፡ አቡሁ ፡ ወመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ በሥልጣኑ ፡
ፈቲሆ ፡ ማዕሠሮ ፡ ለሞት()” ፡ እንዳለ ፡ ድርሳነ ፡ ማኅየዊ() ፡፡ በ3ቱም ፡
ሥልጣን ፡ እንደተነሣ ፡ ሊቃውንቱ ፡ በዝርዝር ፡ ተናረዋል ፡፡
በአብ
፡ ሥልጣን ፡ እንደተነሣ ፡ ቅዱስ ፡ ጳውሎስ ፡ “አብ ፡ አንሥኦ ፡ ለወልዱ ፡ እሙታን” ፡ ብሏል ፡፡ በገዛ ፡ ሥልጣኑ ፡ እንደተነሣ
፡ ቅዱስ ፡ ቄርሎስ ፡ “ወተንሣእኩ ፡ በሥልጣነ ፡ ባሕቲትየ” ፡ ብሏል ፡፡ በመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ሥልጣን ፡ እንደተነሣ ፡ ባስልዮስ
፡ ዘቂሣርያ ፡ “ወተንሥአ ፡ በኃይለ ፡ መለኮቱ” ፡ ብሏል(ሃይ.አበው
፡ ምዕ ፡ 34 ፡ ክ
፡ 5 t ፡ 18) ፡፡
ኃይል ፡ የተባለ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ እንደሆነ ፡ ለማጠየቅ ፡ ወንጌለ ፡ ሉቃስ(ምዕ ፡ 24 ፡ t ፡ 49) ፡
“ወናሁ ፡ እፌኑ ፡ ተስፋሁ ፡ ለአቡየ(እኔም ፡ ተስፋ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስን ፡ እልክላችኋለሁ) ፡ ወአንትሙሰ ፡ ንበሩ ፡ ሀገረ
፡ ኢየሩሳሌም ፡ እስከ ፡ ትለብሱ(እናንተ ፡ ግን ፡ ከሰማይ ፡ ሀይልን ፡ ማለት ፡ ሰማያዊ ፡ ሀብትን ፡ እስክትለብሱ ፡ በኢየሩሳሌም
፡ ኑሩ)” ፡ ብሏል ፡፡ይህስ ፡ ይሁን ፡ በሥልጣነ ፡ ባሕቲትየ ፡ ማለቱ ፡ በብቻየ ፡ ሲል ፡ አይደለምን? ፡ ቢሉ ፤ ይህስ
፡ ትንሣውን ፡ ሲያይ ፡ የተናረው ፡ ነው ፡፡ ማለትም ፡ አብና ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ እንደሱ ፡ ሰው ፡ አልሆኑም ፤ እሱ ፡
ግን ፡ ሰው ፡ የሆንኩ ፣ ከሙታን ፡ የተነሣሁ ፡ በተለየ ፡ አካሌ ፡ እኔ ፡ ብቻ ፡ ነኝ ፡ ሲል ፡ “ወተንሣእኩ ፡ በሥልጣነ
፡ ባሕቲትየ” ፡ አለ ፡ እንጅ ፡ ከአብና ፡ ከመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ የተለየ ፡ ሥልጣን ፡ አለኝ ፡ ሲል ፡ አይደለም ፡፡
ዳግመኛም
፡ የጸጋ ፡ ልጅ ፡ የግድ ፡ ይታመማል ፣ የግድ ፡ ይሞታል ፡ እንጅ
፡ በፈቃዱ ፡ አይታመምም ፣ በፈቃዱ ፡ አይሞትም ፤ እርሱ ፡ ግን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅ ፡ ነውና ፡ በፈቃዱ ፡ ታመመ ፡ ሞተ ፤
“ሞተ ፡ በፈቃዱ ፡ ወተቀብረ ፡ በሥምረቱ” ፡ እንዳለ ፡ ዮሐንስ ፡ ነባቤ ፡ መለኮት ፡፡ ዳግመኛም ፡ የጸጋ ፡ ልጅ ፡ የራሱን
፡ ይታመማል ፡ ይመሞታል ፤ “እመሰ ፡ ኀደረ ፡ ቃል ፡ ላዕሌሁ ፡ ከመ ፡ ኵሎሙ ፡ ነቢያት ፡ ለምንትኑ ፡ ኢተብህለ ፡ በእንተ
፡ ግብሮሙ ፡ እምልደቶሙ ፡ እስከ ፡ ዕለተ ፡ ሞቶሙ ፡ ኮነ ፡ በእንቲአነ ፡ አላ ፡ በእንተ ፡ ርእሶሙ ፡ ባሕቲቶሙ(በነቢያት
፡ ሁሉ ፡ እንዲያድር ፤ ቃል ፡ ከአደረበት ፡ ከተወለዱ ፡ ጀምሮ ፡ እስከ ፡ ሞታቸው ፡ ድረስ ፡ የሠሩት ፡ ሥራ ፡ እኛን ፡
ለማዳን ፡ ተደረገ ፡ ለምን ፡ አልተባለም? ፡ ራሳቸውን ፡ ብቻ ፡ ለማዳን ፡ እንደሆነ ፡ ተነገረ ፡ እንጅ ፡፡
እመሰ
፡ ኀደረ ፡ ላዕሌሁ ፡ ቃል ፡ ከመ ፡ ኩሎሙ ፡ ነቢያት(በነቢያት ፡ ሁሉ ፡ እንዲያድር ፡ ቃል ፡ ከአደረበት) ፤ ለምንትኑ ፡
ተብህለ ፡ በእንተ ፡ ዝንቱ ፡ ባሕቲቱ ፡ ዘተወልደ ፡ እምእግዝእትነ ፡ ቅድስት ፡ ድንግል ፡ ማርያም ፡ ምዕረ ፡ ቦአ ፡ ውስተ
፡ ዓለም ፡ በደኃሪ ፡ መዋዕል(ከእግዝእትነ ፡ ማርያም ፡ ስተወለደ ፡ ስለእርሱ ፡ ብቻ ፡ 5500 ፡ ዘመን
፡ ሲፈጸም ፡ አንድ ፡ ጊዜ ፡ ሰው ፡ ሁኖ ፡ ተወለደ ፡ ተብሎ ፡ ለምን ፡ ተነገረ)” ፡ እንዳለ ፡ አትናቴዎስ(ሃይ.አበው ፡
ምዕ ፡ 31 ፡ t ፡ 31-32) ፡፡
ጌታ ፡ ግን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅ ፡ የባሕርይ ፡ አምላክ ፡ ነውና ፡ ለሰው ፡ ብሎ ፡ ታመመ ፡ ሞተ ፤ “ሞተ ፡ ከመ ፡ ያሕይዎሙ ፡ ለምውታን” ፡ እንዳለ ፡ ዮሐንስ ፡ ነባቤ ፡ መለኮት ፡፡
ምነዋ
፡ የጸጋ ፡ ልጆች ፡ ጻድቃን ፣ ሰማዕታት ፡ መታመማቸው ፣ መሞታቸው ፡ በፈቃዳቸው ፡ አይደለምን?፡ እንደምን ፡ የግድ ፡ ይሆናል?
፡ ቢሉ ፡ ጌታ ፡ ሲአስተምር ፡ በወንጌለ ፡ ማቴዎስ(ምዕ ፡ 1 ፡ t ፡ 36)
፡
ላይ ፡ “ዘኢሐደገ ፡ አባሁ ፡ ወእሞ ፣ ቤቶ ፡ ወዉሉዶ ፡ ወዘኢፆረ ፡ መስቀለ ፡ ሞትየ ፡ ኢይክል ፡ ይፀመደኒ” ፡ ብሎ ፡
እንደገለጸው ፤ እናት ፡ አባቱን ፣ ቤት ፡ ንብረቱን ፡ ትቶ ፡ እኔን ፡ ያልተከተለ ፡ ከእኔ ፡ አንድነት ፡ የለውም ፡ መንግሥተ
፡ ሰማያትን ፡ እንኳንስ ፡ ሊገባባት ፡ አያያትም ፡ ብሎ ፡ አዋጅ ፡ ተናግሯል ፡፡ ጻድቃን ‹ ሰማዕታትም ፡ ይህ ፡ አዋጅ ፡
ግድ ፡ ብሏቸው ፡ ይታመማሉ ፡ ይሞታሉ ፡ እንጅ ፡ በፈቃዳቸው ፡ አይታመሙም ፡ አይሞቱም ፤ እሱ ፡ ግን ፡ ይጸድቅበታል ፡ እንዳይባል
፡ በባሕርዩ ፡ ጻድቅ ፤ ይብርበታል ፡ እንዳይባል ፡ የባሕርይ ፡ ክቡር ፡ ነውና ፡ ለሰው ፡ ሲል ፡ በፈቃዱ ፡ ታመመ ፡ ሞተ
፡:
ዳግመኛም
፡ የጸጋ ፡ ልጅ ፡ አይሰገድለትም ፡ “ዘሰገደ ፡ ለፍጡር ፡ ርጉም ፡ ውእቱ” እንዲል ፤ እሱ ፡ ግን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅ ፡
ነውና ፡ ይሰገድለታል ፡፡ “እመቦ ፡ ዘኢይሰግድ ፡ ለዘተሰቅለ ፡ ውጉዘ ፡ ለይኩን (ለተሰቀለው ፡ የማይሰግድ ፡ ቢኖር ፡ የተወገዘ
፡ ይሁን) ፤ ወይትኈለt ፡ ምስለ
፡ ቀታልያነ ፡ እግዚእ (ጌታችንን ፡ ከሰቀሉት ፡ ከአይሁድ ፡ ጋር ፡ ይቈጠር)” እንዳለ ፡ ጐርጐርዮስ ፡ ነባቤ ፡ መለኮት(ሃይ.አበው
፡ ምዕ ፡ 61 ፡ ክ
፡ 4 ፡ t ፡ 26) ፡፡
መናፍቃን
፡ የጸጋ ፡ አምላክ ፡ ነው ፡ ካሉት ፡ “ዘኢሰገደ ፡ ለዘተሰቅለ ፡ ውጉዘ ፡ ለይኩን” ፡ ያለውን ፡ ምን ፡ ብለው ፡ ይተረጕሙታል?
፡ ቢሉ ፤ በሰውነቱ ፡ ለሞተው ፡ በአምላክነቱ ፡ ያላመነበት ፣ በሰውነቱ ፡ ለተሰቀለው ፡ በአምላክነቱ ፡ ያልሰገደለት ፡ ርጉም
፡ ነው ፡ ሲል ፡ ነው ፡ ብለው ፡ ይተረጕሙታል ፡፡ እኒህ ፡ በምን
፡ ይረታሉ? ፡ ቢሉ ፤ ወልድን ፡ በሰውነቱ ፡ የጸጋ ፡ ልጅ ፡ ነው ፡ ካላችሁ ፡ አይሁድ ፡ ሰቀሉት ፡ ትላላችሁ? ፡ ወይስ
፡ አትሉም? ፡ ብሎ ፡ ይጠይቋል ፡፡ እነሱም ፡ ሰቀሉት ፡ ብለው ፡ ይመልሳሉ ፡፡ ሰቀሉት ፡ ካላችሁ ፡ “ዚሰገደ ፡ ለዘተሰቅለ
፡ ውጉዝ ፡ ውእቱ ፡ ወይትኈለቈ ፡ ምስለ ፡ ቀታልያነ ፡ እግዚእ(በተሰቀቀለው ፡ ያላመነበት ፡ አምላክን ፡ ከሰቀሉት ፡ ከአይሁድ
፡ ጋር ፡ ይቈጠራል) ፤ ይህን ፡ ጊዜ ፡ አምላክነት ፡ የሌለው ፡ የጸጋ ፡ ልጅማ ፡ ቢሆን ፡ ኖሮ ፡ “ወይትኈለቈ ፡ ምስለ
፡ ቀታልያነ ፡ ሰብእ” ፡ ባለ ፡ ነበር ፡ እንጅ ፤ “ምስለ ፡ ቀታልያነ ፡ እግዚእ” ፡ ባለ ፡ ነበርን? ፡ ሲሏቸው ፡ በዚህ
፡ ይረታሉ ፡፡
አስተውሉ
፡ ወንድሞችና ፡ እህቶች ፡ የካሮቹ ፡ መውደቅ ፡ ከዚህ ፡ ይጀምራል ፤፡ እስከ ፡ አሁን ፡ ድረስ ፡ ያለውን ፡ ባለማየታቸው
፡ ከማይወጡበት ፡ ገደል ፡ ተንኮታኩተው ፡ ወድቀዋል ፡፡
ካሮቹ
፡ እንደ ፡ ቅድመ ፡ አያታቸው ፡ ልዮን ፡ ላይመለሱ ፡ የሞቱበት ፡ ቃል ፡ ወልደ ፡ አብ ፡ ላይ ፡ እንደተጻፈው ፡ “ምነው
፡ መሰገዱ ፡ የባሕርይ ፡ ልጅነቱን ፡ ያጠይቃል ፡ ማለት ፡ እንዴት ፡ ነው ፤ ለእግዝእትነ ፡ ማርያም ፡ ለመስቀል ፡ ይሰገድላቸው
፡ የለምን ፤ ክብራቸውስ ፡ የጸጋ ፡ አይደለምን ፡ ቢሉ ፡ ለእግዝእትነ ፡ ማርያም ፡ መሰገዱ ፡ የእሱን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅነት
፡ ያጠይቃል ፡፡ እንዴት ፡ ቢሉ ፡ የጻድቃን ፡ እናቶች ፡ ይሰገድላቸዋልን ፤ ስንኳንስ ፡ ለናቶቻቸው ፡ ለርሳቸው ፡ አይሰገድላቸውም
፤ እርሷ ፡ ግን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅ ፡ የሆነውን ፡ ብትወልድ ፡ እሰግድ ፡ ለእግዝእትነ ፡ ማርያም ፡ ንጽሕተ ፡ ሥጋ ፡ ወነፍስ
፡ ተብሎ ፡ ይሰገድላታል ፡ ሰጊድ ፡ ወክብር ፡ ይደልዋ ፡ ለእግዝእትነ ፡ ማርያም ፡ ወለደ ፡ ማቴዎስ ፡ ፍሥሓ ፡ እንዳለ ፡
ጊጋር ፡ በነገረ ፡ ማርያም ፤ ለመስቀል ፡ መሰገዱ ፡ የእሱን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅነት ፡ ያጠይቃል ፡ እንዴት ፡ ቢሉ ፤ እንግዲያው
፡ የቅዱስ ፡ ጴጥሮስ ፡ የቅዱስ ፡ ጊዮርጊስ ፡ መስቀል ፡ ይሰገድለታልን ፤ ስንኳንስ ፡ ለመስቀሉ ፡ ለርሳቸው ፡ አይሰገድላቸውም
፤መስቀል ፡ ግን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅ ፡ የሆነው ፡ ሥጋው ፡ ቢፈስበት ፤ ደሙ ፡ ቢፈስበት ፡ “እሰግድ ፡ ለመስቀለ ፡ እግዚእነ
፡ ኢየሱስ ፡ ክርሰቶስ ፡ ዘተቀደሰ ፡ በደሙ ፡ ክቡር” ፡ ብለን ፡ እንሰግድለታለን”›››››››ወልደ ፡ አብ ፡ ገፅ ፡
251 ›››››››የሚል ፡ ሀሳብ ፡ አለ ፡ እኒህ ፡ ዓይን ፡ እያላቸው ፡ የማያዩ ፤ ጆሮ ፡ እያላቸው ፡ የማይሰሙ ፤ ልቡና
፡ እያላቸው ፡ የማያስተውሉ ፡ ቤተ ፡ አይሁድ ፤ ይህችን ፡ ያስቀመጥኳትን ፡ ሀሳብ ፡ ብቻ ፡ ቁርጥ ፡ ቁምጥ ፡ አድርገው ፡
እየተመለከቱ ፡ ወደቅ ፤ መውደቅ ፡ ብቻም ፡ አይደል ፡ ብዙ ፡ ኦርቶዶክሳውያንን ፡ ይዘዋቸው ፡ ወደቁ ፡፡ አምላከ ፡ ቅዱሳን
፡ ልቡና ፡ ይስጣቸው ፡፡ ከላይ ፡ በባለፈው ፡ በክፍል ፡ አንድ ፡ ላይ ፡ የጻፍኩትን ፤ እሆም ፡ ከአሁን ፡ ከዚህ ፡ በታች
፡ የምጽፈውን ፡ ሳይመለከቱ ፡ ከመሐል ፡ ላይ ፡ ቁርጥ ፡ አድርገው ፡ ወስደው ፤ ስግደት ፡ አይባም ፡ አላችሁ ፡ እያሉ ፡
የሞኝ ፡ የጨዋ ፡ ንግግር ፡ ሲናገሩ ፡ መስማት ፤ በእነሱ ፡ ድንቁርና ፡ ምን ፡ ያህል ፡ ሰው ፡ ወደ ፡ ሲዖል ፡ እየተጓዘ
፡ እንደሆነ ፡ ማስታወስ ፡ ይቻላል ፡፡ እኒያ ፡ “ካራ” ፡ ወይም ፡ “መጥባሕት” ፡ ብለው ፡ ስም ፡ ያወጡላቸው ፡ ሰው ፡
ምንኛ ፡ የአዕምሮ ፡ ምጥቀት ፡ አላቸው ፤ እኒህ ፡ ቆራጮች ፡
እየቆማመጡ ፡ ያወጡታል ፡፡ ከላይ ፡ በገጽ 251 ፡ ያለውን ፡ ቃል ፡ ቤተ ፡ አይሁድ ፤ የሚጠቅሱት ፤ “ስንኳንስ ፡ ለናቶቻቸው
፡ ለርሳቸው ፡ አይሰገድላቸውም” ፡ የምትለዋን ፡ ብቻ ፡ ቆርጠው ፡ ይጠቅሱታል ፤ ዝቅ ፡ ብሎ ፡ ያለውን ፡ “እርሷ ፡ ግን
፡ የባሕርይ ፡ ልጅ ፡ የሆነውን ፡ ብትወልድ ፡ እሰግድ ፡ ለእግዝእትነ ፡ ማርያም ፡ ንጽሕተ ፡ ሥጋ ፡ ወነፍስ ፡ ተብሎ ፡
ይሰገድላታል ፡ ሰጊድ ፡ ወክብር ፡ ይደልዋ ፡ ለእግዝእትነ ፡ ማርያም ፡ ወለደ ፡ ማቴዎስ ፡ ፍሥሓ ፡ እንዳለ ፡ ጊጋር ፡ በነገረ
፡ ማርያም” ፡ የሚለውን ፡ ቃል ፡ ቢጠቅሱት ፡ ኖሮ ፤ አብዝው ፡ ባልካዱ ፡ ለጻድቃን ፡ አይሰገድላቸውም ፡ የተባለው፡ የትኛዉ
፡ ስግደት ፡ እንደሆነ ፡ ይገባቸው ፡ ነበር ፡፡ ነገር ፡ ግን ፤ እኒህ ፡ ቤተ ፡ አይሁድ ፡ የራሳቸው ፡ ምንፍቅና ፡ ናላቸውን
፡ ያዞራቸው ፡ ስለሆኑ ፤ እነሱ ፡ እየቆራረጡ ፡ እየቆማመጡ ፡ ሲጠቅሱ ፡ በእነሱ ፡ ቤት ፡ ጽድቅ ፡ ነው ፤ ፕሮቴስታንቱ ፡
እየቆማመጠ ፡ እየቆራረጠ ፡ ሲጠቅስ ፡ ግን ፡ ጽድቅ ፡ ነው ፡፡ ለማንኛውም ፡ ካሮችም ፡ ይሁኑ ፡ ፕሮቴስንቶቹ ፡ ቆርጦ ፡
ቆምጦ ፡ በመጥቀስ ፤ አንድ ፡ ዓይነት ፡ ናቸው ፡፡ መልዕክቴ ፡ እንዳይበዛ ፤ ወደ ፡ ሀሳቤ ፡ ልመለስ ፤
እኒህ
፡ ልሙጥ ፡ ሰዎች ፡ የቆረጡት ፡ ቃል ፡ ከነ ፡ ሙሉ ፡ ማብራያው ፡ ሲቀርብ ፡ እንደሚከተለው ፡ ነው ፡፡ በወልደ ፡ አቡ ፡
ላይ ፡ የተጠቀሰው ፡ ሀሳብ ፡ በሰፊው ፡ ሲብራራና ፡ ሲዘረዘር ፤ ለእሱ ፡ መሰገዱ ፡ የባሕርይ ፡ ልጅነቱን ፡ ያጠይቃል ፡
ማለት ፡ እንዴት ፡ ነው? ፤ ስግደትማ ፡ ለእግዝእትነ ፡ ማርያም ፣ ለመስቀል ፡ ይሰገድላቸው ፡ የለምን? ፡ ክብራቸውስ ፡ የጸጋ
፡ አይደለምን? ፡ እንደምን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅነቱን ፡ ያጠይቃል ፡ ተባለለት? ፡ የሚል ፡ ሰው ፡ ቢኖር ፤ ማንኛውም ፡ ክርስቲያን
፡ በማንኛውም ፡ ወደ ፡ ቅድስት ፡ ቤተ-ክርስቲያን ፡ ሲገባ ፤ 5 ት ፡
ስግደት ፡ ይሰግዳል ፤ 3ት ፡ ለሥላሴ ፤
2
፡ ለመስቀልና ፡ ለእግዝእትነ ፡ ማርያም ፡ ስለዚህም ፤ ለእግዝእትነ
፡ ማርያም ፡ እና ፡ ለመስቀል ፡ የጸጋ ፡ ስግደትን ፡ እንሰግድላቸዋለን ፤ ለእነሱ ፡ የጸጋ ፡ ስግደትን ፡ መስገዳችን ፡ የእሱን
፡ የባሕርይ ፡ ልጅነት ፣ የባሕርይ ፡ አምላክነት ፡ ያጠይቃል ፡፡ እንደምን ፡ ያጠይቃል? ፡ ብንል ፡ የባሕርይ ፡ የሆነውን
፡ አምላክ ፡ ወልደ ፡ አምላክ ፡ ብትወልድ ፡ “እሰግድ ፡ ለእግዝእትነ ፡ ማርያም ፡ ድንግል ፡ ወላዲተ ፡ አምላክ ፡ ንጽሕተ
፡ ሥጋ ፡ ወነፍስ” ፡ ብለን ፡ እንሰግድለታለን ፡፡ “ሰጊድ ፡ ወክብር ፡ ይደልዋ ፡ ለእግዝእትነ ፡ ማርያም ፡ ወለደ ፡ ማቴዎስ
፡ ፍሥሐ” ፡ እንዳለ ፡ ጊጋር ፡ በነገረ ፡ ማርያም ፡፡ ለመስቀልም ፡ መሰገዱ ፡ የባሕርይ ፡ ልጅ ፡ የባሕርይ ፡ አምላክ ፡
የሆነ ፡ ወልደ ፡ እግዚአብሔር ፡ ሕያው ፡ ወልደ ፡ ማርያም ፡ ሥግው ፡ መድኅነ ፡ ዓለም ፡ ኢየሱስ ፡ ክርስቶስ ፡ ሥጋው ፡
ቢቈረስበት ፡ ደሙ ፡ ቢፈስበት ፡ “እሰግድ ፡ ለመስቀለ ፡ እግዚእነ ፡ ኢየሱስ ፡ ክርሰቶስ ፡ ዘተቀደሰ ፡ በደሙ ፡ ክቡር”
፡ ብለን ፡ እንሰግድለታለን ፡፡ ለመስቀል ፡ መሰገዱ ፡ የእሱን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅነቱን ፡ ያጠይቃል ፡ ማለት ፡ ስለዚህ ፤
ነው ፡፡
ምነዋ
፡ ለእግዝእትነ ፡ ማርያም ፡ መሰገዱ ፡ የእሱን ፡ የባሕርይ ፡ ልጅነት ፡ ያጠይቃል ፡ ማለት ፡ እንዴት ፡ ነው? ፡ የጻድቃን
፡ እናቶችስ ፡ ይሰገድላቸው ፡ የለምን? የእግዝእትነ ፡ ማርያምስ ፡ ከእነሱ ፡ በምን ፡ ይለያል? ፡ የሚል ፡ ቢኖር ፤ ለጻድቃንስ
፡ እንኳንስ ፡ ለእናቻቸው ፡ ይቅርና ፡ ለእነሱም ፡ ቢሆን ፡ ለእመቤታችን ፡ የምንሰግደውን ፡ ስግደት ፡ አንሰግድላቸውም ፡፡
ይህ ፡ ሲባል ፡ ግን ፡ ከላይ ፡ የያዝነው ፡ ምሥጢር ፡ የባሕርይና ፡ የጸጋ ፡ መሆኑን ፡ ለመለየት ፡ እንጅ ፤ ለጻድቃን ፡
ለቅዱሳን ፡ ስግደት ፡ አይገባም ፡ ማለት ፡ አይደለም ፡፡ ማለትም ፡ ለጻድቃን ፡ ስግደት ፡ ስንሰደግድላቸው ፡ ወላድያነ ፡
አምላክ ፡ ብለን ፡ አይደለምና ፡ አይሰገድላቸውም ፡ መባሉ ፡ “ወላድያነ ፡ አምላክ” ፡ ተብሎ ፡ የሚሰገድላቸው ፡ አለመሆኑን
፡ ለማጠየቅ ፡ ሲሆን ፤ እግዝእትነ ፡ ማርያም ፡ ግን ፡ የባሕርይ ፡ አምላክ ፡ የባሕርይ ፡ ልጅ ፡ ጌታ ፡ መድኃኔ ፡ ዓለምን
፡ በድንግና ፡ ፀንሳ ፡ በድንግልና ፡ የወለደች ፡ በመሆኗ ፡ “እሰግድ ፡ ለእግዝእትነ ፡ ማርያም ፡ ድንግል ፡ ወላዲተ ፡ አምላክ
፡ ንጽሕተ ፡ ሥጋ ፡ ወነፍስ” ፡ ብለን ፡ እንሰግድላታለን ፤ ለጻድቃን ፡ እናቶችም ፡ ይሁን ፡ ለእሳቸው ፡ ንጽሐ ፡ ሥጋ ፡
ቢኖራቸው ፡ እንጅ ፡ በሁለት ፡ ወገን ፡ ደናግላን ፡ ብሎም ፤ እንደ ፡ እመቤታችን ፡ አምላንክ ፡ የወለዱ ፡ አይደሉምና ፡
ለእመቤታችን ፡ የሰገድነውን(ንሰግድ ፡ ለእግዝእነ ፡ ማርያም ፡ ድንግል ፡ ወላዲተ ፡ አምላክ ፡ ብለን ፡ እንደምንሰግደው ፤
ሁሉ) ፡ ለእነሱም ፡ “ወላድያነ ፡ አምላክ” ፡ ብለን ፡ አንሰግድም ፡ ማለት ፡ እንጅ ፡ ስግደት ፡ አያስፈልጋቸውም ፡ ለማለት
፡ አይደለም ፡፡
ምስጋና
፡ ለአንዱ ፡ አምላክ ፡ ለቅድስት ፡ ሥላሴ
ክብር
፡ ለወላዲተ ፡ አምላክ ፡ ለድንግል ፡ ማርያም
ክብር
፡ ለመስቀለ ፡ ክርስቶስ ፡ እጸ ፡ መድኃኒት ፡ ኃይልነ ፡ ወጸወንነ
ስለመስቀል
፡ ይቀጥላል ፡፡
በካሮቹ
፡ እብደትና ፡ ውድቀት ፡ እኔ ፡ ከሚገባኝ ፡ በላይ ፡ እየተናገርኩ ፡ ውስጤ ፡ አላርፍ ፡ ስላለኝ ፤ ከእኔ ፡ የበረታችሁ ፡
ሁላችሁም ፡ በጸሎታችሁ ፡ አስቡኝ ፡፡ እኒህ ፡ የአይሁድ ፡ ትርፎች ፡ ራሳቸው ፡ ቤት ፡ ያለው ፡ የካራ ፡ ዓይነት ፡ ወደ
፡ 5 ፡ የተጠጋ ፡ ሲሆን ፤ ራሳቸው ፡ አንድ ፡ ሳይሆኑ ፡ ኦርቶዶክሳዊት ፡ ቅድስት ፡ ቤተ-ክርስቲያንንና ፡ ኦርቶዶክሳውያን
፡ ሊቃውንትን ፡ እያሳደዱ ፡ ይገኛሉ ፤ ስለዚህ ፡ ምዕመናን ፡ በተዋሕዶ ፡ ስም ፡ ተደብቀው ፡ የሚዘሩት ፡ እርምና ፡ በዚያ
፡ በጉባዔ ፡ ኬልቄዶን ፡ የተደነገገውን ፡ ባህለ ፡ ምንታዌ ፡ እያሽሞነሞኑ ፡ ይዘውት ፡ እንደሚገኙ ፡ አውቀን ፤ ከሱስንዮሳውያን
፡ ዳግም ፡ ጥምቀት (እርምና) ፡ ራሳችነን ፡ ነጻ ፡ እናወጣ ፡ ዘንድ ፡ ጥሪዬን ፡ አስተላፋለሁ፡፡
የሰላም አምላክ ክርስቶስ እውነትን ይግለጽ።
ReplyDelete