Sunday, October 16, 2022

 የተቀብዐ ጾመኞችና ሩጫቸው

=======+=====+=====
ካነበብኩት
  • ====+====
ቄርሎስ ስለ ክርስቶስ ተቀባዒነት ከተናገረው
=====+====+===
“እመ ይሬስዮሙ ለመላእክቲሁ መንፈሰ (መላእክትን በዓይን የማይታዩ በእጅ የማይዳሰሱ ረቂቃን አድርጎ የፈጠራቸው ከሆነ ፤ አንድም የፈጠራቸው ሲሆን) ፤ ወመንበር ቦቱ ዘመለኮት (የአምላክነት ሥልጣን ገንዘቡ ከሆነ ፤ አንድም ገንዘቡ ሲሆን) ፤ በእንተ ምንት ተቀብዐ ቅብዓ ትፍሥሕት (እንደምን የደሥታ ዘይትን ተቀባ/ከበረ ብትል) ፤ ወይፈጥር መላእክተ ከመ አምላክ ውእቱ (የባሕርይ አምላክ ነውና መላእክትን ፈጠረ) ፤ ወተቀብዓ ከመ ሰብእ (ሰው በመሆኑ ተቀባ ከበረ) ፤ አኮ በህላዌ መለኮት (በባሕርየ መለኮቱ አይደለም) ፤ አላ ተሰጊዎ ነሥአ ቅብዓተ በሥምረቱ አምላክ ወሰብእ ክርስቶስ (በፈቃዱ ሰው በሆነ ጊዜ ተቀባ ከበረ ተባለ እንጅ ፤ ክርስቶስ አምላክ ነው ሰውም ነው እልሃለው)”
ብራና ምቅዋም 20 ላይ ይገኛል ፡፡ ምቅዋም ማለት ምዕራፍ እንደማለት ነው ፡፡
ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ ባሳተሙት ላይደግሞ ምዕራፍ 56 ላይ የሚገኝ ሲሆን
ቅብዓትን ስለሚጾሙ
“በእንተ ምንት ከብረ ክብረ ትፍስሕት” ብለው ዘሩን ቀይረውታል ፡፡ ዘሩን ከለወጡ በኋላ ከአብ የተገኘ ክብርም አካለ ቃል ነው ፤ ክብርነቱም ለተዋሐደው ሥጋ ነው በማለት የቃልንና የሥጋን ተዋሕዶ የሚያፈርስ ምንታዌን አሰልጥነዋል፡፡
እሳቸው ተቀብዐን ለማምለጥ እንዲህ ቢንፈራገጡም “ወተቀብዐ ከመ ሰብእ” በማለት ወገብ ዛላቸውን ብሎ ያሳርፋቸዋል ፡፡ እንዴት አትልም ወዳጄ!!! በእሳቸው ቤት ተቀብዐ የተባለ ሥጋ ነው ፤ ቄርሎስ ደግሞ “ወተቀብዐ ከመ ሰብእ” ያለው ሥግው ቃልን ነው ፡፡ በዚህም መሠረት ቃል ክብር ከሆነ; ለሥጋ “ከመ ሰብእ” የሚለው አንቀጽ አይስማማውም ፤ ምክንያቱም ሥጋ ጥንቱንም ሰው ነውና ለሥጋ እንደ ሰው (ሰው በመሆኑ) አይባልለትምና በዚህ ሽንጣቸውን ቆርጦ ይጥላቸዋልና ያሳርፋቸዋል ማለት ለዚህ ነው ፡፡ በቀጣይ እድሜና ጤና ይስጠን እንጅ ብዙ እጽፋለሁ ፡፡ እንነጋገራለን ፡፡ በመጽሐፍም ከች ማለታችን አይቀርም ፡፡
====+====+====+====
ዘር ቢቀይሩ ግስ ቢለዋውጡ እየነቃቀሉ ቢጥሉት ያው ክርስቶስ ማለት የተቀባ ቅቡዕ ማለት መሆኑን ስለማይለቅላቸው ማምለጫ የላቸውም
እየተከተሉ በተቀብዐ ጅራፍ ሰኮና ሰኮናቸውን መጥበስ ነው የት አባታቸውና ፡፡
ወይ ተቀብዐ ይኸን አውደልዳይ ሁሉ እንዲህ ያሯሩጠው ፡፡
እኔ የፈለሰፍኩት እንዳይመስላችሁ ከታች ያለውን የብራና ድርሳን በፎቶ ተመልከቱና አመሳክሩት (በተለይ በተለይ እነ ምላስ ብቻ)
ከፎቶው ላይ አውራ ጣት ካለበት ላይ በቀይ “እመጽሐፈ ዕብራዊያን” ተብሎ ከተጻፈው ጀምራችሁ እዩት ፡፡



No comments:

Post a Comment