Monday, September 27, 2021

 

ኤዎስጣቴዎስ ከፋሌ ባሕር

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ!


አንተ ት(ኮ)ንን ኃይለ ባሕር---ውቅያኖስን የምትገዛ አንተ ነህ ፤ ወአንተ ታረምሞ ለድምፀ ማዕበላ---እስከ ዝየ ብጽሒ ብለህ የውቅያኖስን ማዕበል ሞገዷን ፀጥ የምታደርገው አንተ ነህ ፡፡
  አንተ አኅሠርኮ ለዕቡይ ከመ ቅቱል--- ሌዋታንን እንደሞተ ያዋረድከው አንተ ነህ ማለት በባሕር ተወስኖ እንዲኖር  ያደረግኸው  አንተ ነህ”   መዝ   88 9-10

====================================

አመ አሥሩ ወሰሙኑ ለመስከረም በዛቲ ዕለት አዕረፈ ኤዎስጣቴዎስ መምህረ ሃይማኖት ወሰባኬ ወንጌል (አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መስከረም ዐሥራ ስምንት በዚህች ቀን ወንጌልን የሚሰብክ  የሃይማኖት መምህር አባታችን ኤዎስጣቴዎስ አረፈ) ፡፡

Sunday, September 5, 2021


 


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ!!!

========+++======+++=====+++========

መሢሐውያን ወንድም እህቶቼ እናት አባቶቼ እንደምን አላችሁ? 

በዛሬው መልዕክቴ የ2014 ዓ.ም ምህረት ዘመን በዓላትና አጽዋማት የሚውሉባቸውን የባሕረ-ሐሳብ ቀመሮችን ቀለል ባለ አቀራረብ ይዤላችሁ መጥቻለሁ ፡፡

=======+++=========+++=========

ለመግቢያ ያህል ነቢየ እግዚአብሔር ክቡር ዳዊት ስለዘመን መቀያየርና ዘመንን ሲለሚለውጠው የዘመናት ባለቤት እንዲህ ሲል የተናገረውን ላስነብባችሁ ወደድኩ፡፡

==========+++========+++========

“ሐወጽካ ለምድር ወአርወይካ ( ይህችን ዓለም በረድኤት ጎበኘሃት አንድም ኢየሩሳሌምን ከሰብዓ ዘመን በኋላ በረድኤት ጎበኘሃት ፤ ማለት የዘሩባትን እንድታበቅል የተከሉባትን እንድታጸድቅ አደረግሃት) ፤ አንድም ትሩፍን ከሰብዓ ዘመን በኋላ በረድኤት ጎበኘኻት) ፤ አንድም ምእመንን ከአምስት ሽህ አምስት መቶ ዘመን በኋላ በልጅነት ጎበኘሃት፡፡

 ወአብዛኅኮ ለብዕላ (የዚህችን ዓለም አንድም የኢየሩሳሌምን ብዕለ ሥጋዋን አበዛኸው)    አንድም ብዕለ ሥጋዌን አበዛኸው ፤ አንድም ብዕለ ነፍሷን አበዛኸወ ፡፡