“ኤዎስጣቴዎስ ከፋሌ ባሕር”
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ!
አንተ ት(ኮ)ንን ኃይለ ባሕር---ውቅያኖስን የምትገዛ አንተ ነህ ፤ ወአንተ ታረምሞ ለድምፀ ማዕበላ---እስከ ዝየ ብጽሒ ብለህ
የውቅያኖስን ማዕበል ሞገዷን ፀጥ የምታደርገው አንተ ነህ ፡፡ አንተ አኅሠርኮ ለዕቡይ ከመ ቅቱል--- ሌዋታንን እንደሞተ ያዋረድከው አንተ ነህ ማለት በባሕር ተወስኖ እንዲኖር ያደረግኸው አንተ ነህ” መዝ 88፥ 9-10
====================================
አመ አሥሩ ወሰሙኑ ለመስከረም በዛቲ ዕለት አዕረፈ ኤዎስጣቴዎስ መምህረ ሃይማኖት ወሰባኬ ወንጌል (አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መስከረም ዐሥራ ስምንት በዚህች ቀን ወንጌልን የሚሰብክ የሃይማኖት መምህር አባታችን ኤዎስጣቴዎስ አረፈ) ፡፡