Monday, April 17, 2023

ዜና ትንሣኤሁ ለኢየሱስ ክርስቶስ
=======+==========
ክፍል አንድ
====================
እነሆ የክርስቶስን ትንሣኤ የሚያወሱ ዐበይት ቃላትን ከዕለቱ ሥርዓተ ቅዳሴና የዋዜማ ሥርዓት ለአዘክሮት እንመልከት ፡፡
==========================
“የመጀመሪያው (ከቅዳሴ በፊት የሚሰበከው ምስባክ)
==============================
“ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃህ እምንዋም
ወከመ ኃያል ወኅዳገ ወይን
ወቀተለ ጸሮ በድኅሬሁ”
መዝሙር 77 ፡65
አንድምታ ትርጉም
“ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃህ እምንዋም ፤ ወከመ ኃያል ወኅዳገ ወይን ፤ ወቀተለ ጸሮ በድኅሬሁ” ”
የተኛ ሰው ፈጥኖ እንደሚነሳ እግዚአብሔርም ከሰባ ዘመን በኋላ ፈጥኖ በረድኤት ተነሣ
ከመ ዘኃደጎ ሥካረ ወይን ይላል አብነት የወይን ሥካር እንዳለፈለት ሰው አንድም ከመ ኅዱግ ወይን ይላል አበርትቶ እንደተጣላ ወይን ፡፡ በሀገራቸው ፅኑ መጠጥ አለ ሰው የጠጣው እንደሆነ ሦስት ቀን ወድቆ ይሰነብታል ፡፡ በሦስተኛው ቀን ጥዒና (ጤና) አግኝቶ ኃይል ተሰምቶት ይነሣል ፡፡ አንድም ወይ በተተከለ በሦስት ዓመት ዳስ ጥለውት ያፈራል ፡፡ አንድም ወይን በክረምት ወድቆ ይከርማል በበጋ ዳስ ጥለው በዚያ ላይ ያደርጉታል ይለመልማል ያብባል ያፈራልም ፡፡ ጌታም ቱሩፋንን ይዞ ከባቢሎን ወጥቷልና ፡፡
በእስራኤል ከፈረደ በኋላ በአሕዛብ ፈረደባቸው ፡፡ አንድም እስራኤልን ተከትለው የመጡ ግብጻውያንን አሰጠመ ፡፡
አንድም በዘድኅሬሁ ይላል አብነት ወደኋላው በተመለሰ ውኃ ግብጻውያንን አጠፋቸው ፡፡
አንድም ወተንሥአ ይላል
ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በከርሠ መቃብር አድሮ ተነሣ
ወከመ ይላል
የወይን ሥካር ያለፈለት ሰው ፈጥኖ እንዲነሣ ጌታም ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በከርሠ መቃብር አድሮ ተነሣ ፡፡
አንድም ከመ ኅዱግ ይላል
አበርትቶ እንደተጣለ ወይን ፤ ያንን ጠጥቶ ወድቆ ይሠነብታል በሢስኛው ቀን ፈጥኖ ይነሣል ፤ ጌታም በሦስተኛው ቀን ፈጥኖ ተነሥቷልና ፡፡
ወቀተለ ይላል
በአዳምና በሔዋን ከፈረደባቸው በኋላ በአጋንንት ፈረደባቸው ፡፡
አንድም በዘድኅሬሁ ይላል
በኋላው በተተከለ መስቀል ዲያብሎስን ድል ነሣው ፡፡ አንድም ተከታይ ጠላት ዲያብሎስን አንድም ታናሽ ጠላት ዲያብሎስን ድል ነሣው ፡፡
በቅዳሴ ሰዓት የሚሰበከው ምስባክ
ዛቲ ዕለት እንተ ገብራ እግዚአብሔር
ንትፈሣሕ ወንትሐሰይ ባቲ
ኦእግዚኦ አድኅንሶ
ይህች ዕለተ ሚጠት እግዚአብሔር አሕዛብን አጥፍቶ ትሩፋንን አውጥቶ ሥራውን የሠራባት ናት ፡፡ አንድም ይች ዕለተ ዐርብ እግዚአብሔር አጋንትን አጥፍቶ ነፍሳትን አውጥቶ ሥራውን የሠራባት ዕለት ናት ፡፡
በሷ ፈጽሞ ደስ ይበለን ፡፡
አቤቱ አድነና ፡፡ አንድም አቤቱ አድነን ፡፡
በቅዳሴ ጊዜ የሚነበበው ወንጌል
የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 20 ፡ 1-19
“ወበእሑድ ሰንበት መጽአት ማርያም መግደላዊት ኀበ መቃብር
በአንድ ሰንበት አንድም በመጀመሪያው ሰንበት እሑድ ሰንበት በተባለበት ቀን ማርያም መግደላዊት ማለዳ ገሥግሣ ወደ መቃብር መጣች ፡፡
እንዘ ዓዲሁ ጽልመት
ገና ጨለማው ሳይለቅ ገና ጨለማ ሳለ ፡፡
ወረከበት ዕብነ እቱተ እምአፈ መቃብር
ደንጊያውን ከመቃብሩ ላይ ተነሥቶ አገኘችው፡፡
ወሮጸት ወበጽሐት ኀበ ስምዖን ጴጥሮስ ወኀበ ዝኩ ካልዕ ረድእ
ከሌለኛው ባለሟሉና ከስምዖን ጵጥሮስ ዘንድ ፈጥና ሄደች ፡፡ባለሟሉ ያለው ራሱ ዮሐንስን ነው ፡፡
ወትሎሙ ነሥእዎ ለእግዚእየ እምውስተ መቃብር
ጌታየን ከመቃብር አውጥተው ወስደውታል ፡፡
ወኢየአምር ኀበ ወሰድዎ
ወደየት እንደወሰዱት ግን አላውቅም ፡፡
መጽኡ ኅቡረ ስምዖን ጴጥሮስ ወዝኩ ካልዕ ረድእ ወሖሩ ኀበ መቃብር
ጴጥሮስና ሌላኛው አገልጋዩ መጥተው ወደ መቃብር ሄዱ ፡፡
ወእንዘ ይረውጹ ክልኤሆሙ ኅቡረ ፡፡
ሁለቱ ፈጥነው እየሮጡ አንድ ሁነው ሲሄዱ
በደሮ ለጴጥሮስ ዝኩ ካልእ ረድእ በጺሐ ኀበ መቃብር ፡፡
ሌላኛው አገልጋይ ጴጥሮስን ቀድሞት ወደ መቃብር ሄደ ፡፡ ስለምን ቀደመው ቢሉ ሕጻን ነው በፍቅሩ ይናደዳልና ፡፡
ወሶበ ሐወጸ ርእየ መዋጥሐ ንቡረ
ዘልቆ በተመለከተ ጊዜ መጎናጸፊያውን አገኘ ፡፡
ወኢቦአ ባሕቱ
ነገር ግን አልገባም ፡፡ ለምን አልገባም ቢሉ ሕጻን ነውና ቢፈራ ፤ አንድም ለክብረ ጴጥሮስ ፤ ከኤጲስ ቆጶስ አስቀድሞ ከመቅደስ እንዳይገባ ፡፡
ወተለዎ ስምዖን ጴጥሮስ ወበጽሐ
ስምዖን ጴጥሮስ ተከትሎት ደረሰ ፡፡ ስለምን ተከትሎት ዘግይቶ ደረሰ ቢሉ አረጋዊ ነውና በኀዘንም ተቀጥቅጧልና ፡፡
ወቦአ ውስተ መቃብር
ወደመቃብሩ ገባ ፡፡
ኤጲስቆጶስ ከቄስ አስቀድሞ መቅደስ እንዲገባ
ወረከበ መዋጥሐ ንቡረ ውስተ አሐዱ ገጽ
መጎናጸፊያውን በአንድ ወገን አገኘ ፡፡
ወሰበነኒ ዘዲበ ርእሱ እንተ ባሕቲቱ ጥብሉለ
ሻሹን እንደተጠመጠመ ለብቻው
ወአኮ ምስለ መዋጥሕ
ከመጎናጸፊያው ጋር ሳይቃወስ
ወእምዝ ቦአ ዝኩኒ ካልእ ረድእ ዘበደሮ በጺሐ ኀበ መቃብር
ከዚህ በኋላ ቀድሞ ከመቃብሩ የደረሰው ሌላኛው አገልጋይ ገባ ፤ ቄስ ኤጲስ ቆጶስን ተከትሎ መቅደስ እንዲገባ ፡፡
ወርእዩ ወአምኑ
ትሣኤውን አይተው አመኑ ፡፡
እስመ ዓዲሁ ኢያእመሩ ዘውስተ መጻሕፍት ዘከመ ሀለዎ ይትነሣእ እምነ ምውታን
ከሙታን ተለይቶ ይነሣ ዘንድ እንዳለው መጻሕፍት የተናገሩትን ገና አላወቁም ነበርና ፡፡
ወእምዝ ሖሩ ክልኤሆሙ አርዳኢሁ
ከዚህ በኋላ ሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ ሄዱ ፡፡
ወአተው ቤቶሙ
ከቤታቸው ገቡ ፡፡
ቁጥር 10
አሜን
ውድ ኦርቶዶክሳውያን እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሳችሁ ፡፡

No comments:

Post a Comment