ዜና ትንሣኤሁ ለኢየሱስ ክርስቶስ
=======+==========
ክፍል ሁለት
======
ከክፍል አንድ በቀጥታ የቀጠለ
====================
ወማርያምሰ ቆመት ኀበ መቃብር አፍአ ወትበኪ
ወእንዘ ትበኪ ሐወጸት ውስተ መቃብር
እያለቀሰች ወደ መቃብር በተመለከተች ጊዜ
ወርእየት ክልኤተ መላእክተ በጸዓድው አልባስ
ሁለት መላእክት ብሩህ ብሩህ (ነጭ ነጭ) ልብስ ለብሰው
ወይነብሩ አሐዱ ትርኣሰ ወአሐዱ ትርጋጸ ኀበ ነበረ ሥጋሁ ለእግዚእ ኢየሱስ
የጌታችን ሥጋ ካለበት ቦታ አንዱ በራስጌ አንዱ በግርጌ ተቀምጠው አየች ፡፡
ወይቤልዋ እሙንቱ መላእክት ምንት ያበክየኪ ኦ ብእሲቶ
እነዚያ መላእክት አንች ሆይ ምን ያስለቅስሻል
ወመነ ተኃሥሢ
ማንንስ ትሻለሽ አሏት ፡፡
ወትቤሎሙ እስመ ነሥእዎ ለእግዚእየ እምውስተ መቃብር
ጌታየን ከመቃብር ውስጥ ወስደውታልና
ወኢየአምር ኀበ ወሰድዎ
ወደየት እንደወሰዱት ግን አላውቅም አለቻቸው ፡፡
ወዘንተ ብሂላ ተመይጠት ድኅሬሃ
ይህንን ተናግራ ወደኋላ ተመለሰች ፡፡ ስለምን ወደኋላ ተመለሰች ቢሉ
የአዘንተኛ ዓይኑ ባካና ነውና ፡፡ አንድም መላእክት ከወደፊቷ ሲሰግዱ አይታቸዋለች ፡፡ ከወደኋላዋ ጥላውን ጥሎባታል ፡፡ መለስ ብትል ቁሞ አይታዋለች ፡፡
ወኢያእመረት ከመ እግዚእ ኢየሱስ ውእቱ
ጌታ ኢየሱስ እንደሆነ አላወቀችውም ፡፡
ወይቤላ እግዚእ ኢየሱስ ብእሲቶ ምንት ያበክየኪ
ጌታ ኢየሱስም አንች ሆይ ምን ያስለቅስሻል
ወመነ ተኃሥሢ
ማንንስ ትሻለሽ (ትፈልጊያለሽ) አላት ፡፡
ወመሰላ ላቲሰ ዓቃቤ ገነት ውእቱ
ለእሷም አታክልት ጠባቂ መስሏት ነበር ፡፡
ወትቤሎ እግዚእየ እመኒ አንተ ነሣእኮ ንግረኒ ኀበ ወሰድኮ
ጌታየን አንተ ወስደኸው እንደሆነ ወደየት እንደወሰድከው ንገረኝ
ከመ እሑር አነ ወአንሥኦ ኀቤየ ከመ ዕቅብዖ ዕፍረተ
እኔም ሂጄ ወደኔ አምጥቼ ሽቱ ዕቀባው ዘንድ አለችው ፡፡
ወይቤላ እግዚእ ኢየሱስ ማርያም
ጌታ ኢየሱስም ማርያም አላት ፤፡
ወተመይጠት ወትቤሎ በነገረ ዕብራይስጥ ረቡኒ
ተመልሳ በዕብራውያንን አነጋገር (ቋንቋ) ረቡኒ አለችው ፡፡
ዘበትርጓሜሁ ሊቅ ብሂል
ትርጓሜውም መምህር ማለት ነው ፡፡
ወይቤላ እግዚእ ኢየሱስ ኢትልክፍኒ እስመ ዓዲ ኢዐረጉ ኀበ አቡየ
የተግሳጽ አነጋገር ነው ፡፡ ወደ አባቴ አልወጣሁም ማለት ገና አላመንሽብኝምና ፡፡ አንድም የመሰናበቻው ጊዜ የደረሰ መስሏት ቀርባለችና የማርግበት (አላረግሁም=ረን አጥብቅ /ዕርገቱን ሲያጠይቅ ነው) ጊዜ ገና ነውና አትንኪኝ አላት ፡፡ ይህም ካህናት ልብሰ ተክህኖ ለብሰው ሳሉ ሊነኳቸው እንዳይገባ ለማጠየቅ ነው ፡፡
ወሑሪ ባሕቱ ኀበ አኃውየ ወበሊዮሙ አዓርግ ኀበ አቡየ ወአቡክሙ ኀበ አምላኪየ ወኀበ አምላክክሙ ፡፡
ወደ ወንድሞቼ ሂጅና ወደ አባቴ ወደ አባታችሁ ወደ አምላኬ ወደ አምላካችሁ (ወደፈጣሪየ ወደፈጣሪያችሁ) ዐርጋለሁ ብለሽ ንገሪያቸው እንጅ አትንኪኝ አላት ፡፡
አቡየ ብሎ ስለልደት ተናገረ
አቡየ ያለው የእሱን የባሕርይ ልደቱን ያጠይቃል ፡፡ አቡክሙ ያለው የኛን የጸጋ ልደት ያጠይቃል ፡፡
አምላኪየ አለ በሥጋ ይፈጥረዋልና አምላክክሙ አለ በጥንተ ተፈጥሮ በሐዲስ ተፈጥሮ ፈጥሮናልና ፡፡
ቁጥር 17 ድረስ
አሜን
================
ከዚህ ላይ አንዳንድ ነጥቦችን እናንሳና ኦርቶዶክሳዊ መሠረታችንን እናጽና ፡፡
================================
መድኅን ክርስቶስ “ኀበ አምላኪያ ወአምላክክሙ--ወደ አምላኬ ወደ አምላካችሁ” ብሎ ተናግሯል ፡፡ ክቡር ዳዊት በትንቢቱ “ቀብዐከ እግዚአብሔር አምላክከ” ብሎ ተናግሯል ፡፡
ክርስቶስ አምላኪየ ብሎ የጠራው እግዚአብሔር አብን ነው ፡፡ አምላኪየ ያለበት ምክንያቱ ደግሞ በሥጋው ፍጡር መሆኑን የሚያጠይቅ ነው ፡፡ አምስት ኪሎ ላይ ያለችዋ መንበረ ፓትርያርክ ላይ ያሉት የሲኖዶስ አባላት ጳጳሳት በ2015 ዓ.ም ጥቅምት ላይ “ወልደ አብ የተባለ መጽሐፍ ወልድን ፍጡር ብሏል” ብለው አውግዘውታል ፡፡ ወልደ አብ የተናገረው መድኅን ክርስቶስ በዮሐንስ ወንጌላዊ አድሮ የተናገረውን ነባራዊ ሐቅ ነው ፡፡ አውጋዞች ዘመዶቻችን ግን ወልድን ፍጡር ይላል ብለው ሲያወግዙ ዮሐንስ ወንጌላዊን ራሱ ክርስቶስን እንዳወገዙት ተረድተውት ይሆን?
ለሁሉም ትንሣኤ ልቡና ያድልልን
እኔና እናንተ ዕዝነ ልቡናችንን በዚህ ምሥጢር ላይ አርፈን ክርስትናችንን እንጠብቅ ዘንድ እንትጋ ፡፡ እውነት ተከታዩአ እጅግ ጥቂት ነው ፡፡ ለዚህም ሰሙነ ሕማማትን ማሰብ እጅግ ከበቂ በላይ ነው ፡፡ በተለይ በተለይ ዕለተ ዓርብ ድንቅ ምሥጢር የተገለጠባት ፡፡ እነ ይሑዳንም እነ ዮሐንስንም በደንብ አድርገን የተመለከትንባት ምሳሌአችን ናት ፡፡
ክቡር ዳዊት አምላክከ ያለውና ክርስቶስ አምላኪየ ብሎ የጠራው እግዚአብሔር አብ ነው ፡፡ ይህ ሁኖ ሳለ ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ “እግዚአብሔር አምላክከ የሚለውን እግዚአብሔር አምላክህ ብለን ከተረጎምነው ለክርስቶስ ሌላ አምላክ አለው ያሰኝብናልና የብሉይ ኪዳን እግዚአብሔርናከ አምላክናከ --እግዚአብሔርነትህ አምላክነትህ ብለን አቅንተን እንተረጉማለን” በማለት ጽፈውልናል (ቃለ ጽድቁ ለአብ 2007 ዓ.ም 2ኛ ዕትም ገጽ 124)፡፡
ሰውየው ተቀብዐ በመቀባቱም ክርስቶስ ተባለ መባሉን ላለማመን ሲሉ እንደዚህ ደንደሳሙን ክሕደት ተናግረውታል ፡፡ የክሕደታቸው ደንደስ ከዮሐንስ ወንጌል ጋር አጣልቶ በራሳቸው መንገድ እንዲጓዙ አደረጋቸው ፡፡ ተቀብዐን አመልጣለሁ ሲሉ የወልድን ሰውነት ፈጽመው አጠፉት ካዱት ፡፡ ከዚያም ወደ ሮማዊቷ ኩትለካ ሽምጥጥ ብለው ሮጡ ፡፡
እንዴት አትሉኝም ወንድም እህቶቼ
ዮሐንስ ጌታችን አምላኬ ማለቱ በሥጋ ስለሚፈጥረው ነው ብሎ ተረጎመው ፡፡ ታዲያ ዮሐንስ ወንጌላዊ የተናገረውን ቃል የሚለውጡና የሚያቃኑት ታላቁ ሊቅ ስምዐኮነ መልአክና እሳቸውን የመሳሰሉቱ ሊቃውንት ከዮሐንስ ወንጌላዊ የተሻለ አረዳድና ዕውቅና ተሰጥቷቸው ይሆንን?ንኅሥሥ፡፡ ወደ አምላክነቴ በማለት ሥጋን ከቃል ለያይቶ ነጣጥሎ መኮትለክ አይደል ይኄ::
ሲቀጥል ክቡር ዳዊት እግዚአብሔር አምላክከ ያለውን እንደነ ሊቀ ሊቃውንት ስምዐኮነ አነጋገር “እግዚአብሔርናከ አምላክናከ” ብለን ከለወጥነው እንደ እሳቸው አነጋገር ደግሞ አቃንተን ከተረጎምነው ፤ በዚህ በዮሐንስ ወንጌል “ኀበ አምላኪየ ወኀበ አምላክክሙ” ያለውን “ኀበ አምላክናየ ወኀበ አምላክናክሙ” ማለት ግዴታችን ይሆናላ! ፤ እንዴት አትሉኝም ባለቤቱ አንድ ነዋ! ፡፡
እንዲህም ብለን እንደነ ሊቀ ሊቃውንት ስምዐኮነ አቃንተን ከተረጎምነው የሚያመጣብን እጅግ ደንደሳም ክሕደት ነው ፡፡
እንዴት ያመጣል ቢሉ ፤
ኀበ አምላክናየ ማለት ወደ አምላክነቴ ማለት ሲሆን ቃል ከሥጋ ጋር ሲዋሐድ አምላኩን አጥቶ ነበርና እንደገና ወደ አምላክነቴ ላርግ አለ ያሰኛልና ፡፡ ዉላጤና ሚጠት የተሰኙ ደንደሶችን ያጎናጽፋልና ፡፡
ሌላውና ዋነኛው ደግሞ በእውነቱ ክቡር ዳዊት “እግዚአብሔር አምላክከ” ብሎ ሲነግረን ምሥጢሩ ሳይገለጥለት ቀርቶ ይሆን እነ ሊቀ ሊቃውንት ስምዐኮነ እና መሰሎቻቸው የብሉይ ኪዳን መምህራን “እግዚአብሔርናከ አምላክናከ” ብለው ሊያቃኑት የቻሉት?ይኸንንም ንኀሥሥ ፡፡
የትንሣኤው ንጉሥ ትንሣኤ ልቡናን ያድለን አሜን!
ይቆየን!
ስብሐት ለእግዚአብሔር ኪያነ ዘፈጠረነ ከመ ናምልኮ
ስብሐት ለማርያም እመ አምላክ እግዝእትነ ወመድኃኒትነ
ስብሐት ለመስቀለ ክርስቶስ ዕፀ መድኃኒት ኃይልነ ወፀወንነ፡፡
ክፍል ሦስት ይቀጥላል ፡፡