የተቀብዐ ጾመኞችና ሩጫቸው
======+====+=====
ካነበብኩት-------3
=======+======+=========
“ዘተወልደ በዳኃሪ መዋዕል በሥጋ ፤ ወተቀብዓ ውስተ ዝንቱ ዓለም በዘይትፌኖ እምኀበ እግዚአብሔር አብ ወተሰምየ ክርስቶስ ፡፡ አኮ በእንተ ካልዕ አላ በእንተ ዘተቀብዓ ፤ እስመ ክርስቶስ ብሂል ቅቡዕ ብሂል ፡፡”
አማርኛ ትርጉም
“በኋላ ዘመን በሥጋ የተወለደ ፤ ከእግዚአብሔር አብ በሚገኝ ክብር በዚህ ዓለም የከበረው ፤ ክርስቶስ የተባለው እርሱ ነው ፡፡ በሌላም አይደለም ስለተቀባ ነው እንጅ ፤ ክርስቶስ ማለት የተቀባ ማለት ነውና”
===========================================
የሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ ትርጉም
“ዘተወልደ በደኃሪ መዋዕል በሥጋ ፤ ወከብረ በዝንቱ ዓለም በዘይትፌኔ እምኀበ እግዚአብሔር አብ፤ ወተሰምየ ክርስቶስ ፤ አኮ በእን ካልዕ ፤ አላ በእንተ በዘተሰብአ ፤ እስመ ክርስቶስ ብሂል አሐዱ እምክልኤቱ ብሂል፤
የአማርኛ ትርጉማቸው፡
“በኋላ ዘመን በሥጋ የተወለደ ፤ ከአብ በሚገኝ ክብር በዚህ ዓለም የከበረው እሱ ነው ፡፡ ከአብ የተገኘም ክብር አካለ ቃል ነው ፡፡ ክርስቶስ ተባለ ፤ በኅድረት አይደለም ፤ ቢዋሐድ ነው እንጅ ፤ ክርስቶስ ማለት በተዋሕዶ ከበረ ማለት ነውና” ብለውታል ፡፡
==========================================
የመጀመሪያው ትክክለኛው ቃል ከታች በብራናው ላይ በፎቶ የምታዩት ነው ፡፡
===========================================
ከሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ ሥራ ላይ እንደምትመለከቱት “ወተቀብዐ” የሚለውን ዘር “ወከብረ” ብለው ለውጠውታል ፡፡ ያው ተቀብዐን በደንብ አድርገው ይጾሟታልና ዘርን በዘር ይለውጣሉ ፡፡
===========================================
ቀጥለውም “ከአብ የተገኘ ክብርም አካለ ቃል ነው” ብለው ምንታዌን ሰተት አድርገው አምጥተዋታል ፡፡ አንባቢው ወዳጄ ሆይ! በትኩረት ተመልከትልኝ ቄርሎስ ከአብ በሚገኝ ክብር ከበረ ያለው ሥግው ቃልን ነው በመክበሩም ክርስቶስ ተባለ ያለው ሥግው ቃልን ነው ፡፡ እንደ ሊቁ አነጋገር ግን ክርስቶስ የተባለው ትስብእት ነው ፡፡ ምክንያቱም ቄርሎስ ከአብ በሚገኝ ክብር በመክበሩ ክርስቶስ መባሉን ተናግሯል ፤ እሳቸው ደግሞ ከአብ የተገኘው ክብር ቃል ነው ብለዋልና ፤ ከአብ በሚገኝ ክብር(በቃል) የከበረው ትስብእት ነውና ፤ ክርስቶስም የተባለው የተቀባው ነውና በእነሱ ቤት ክርስቶስ ማለት ትስብእት ነው ማለት ለዚህ ነው ፡፡ ተቀብዐን ማምለጥ የለም ያው መንፈራገጥ እንጅ ፡፡
===========================================
በጣም የሚደንቀው ደግሞ “ወተቀብዐ” የሚለውን “ወከብረ” ብለው ነበር ያለዘቡት ፡፡
ዝቅ ካሉ በኋላ ግን “አኮ በካልዕ” የሚለውን “በተዋሕዶ ከበረ” ወደሚለው የምንታዌ ትምህርታቸው ለመጎተት እንዲቀናቸው “ካልዕ” የሚለውን ቃል “ኅድረት” ብለው ለወጡት ፡፡ አንባቢው አሁንም መጽሐፍ ቅዱስ እየተለወጠ እንደሆነ በደንብ ተረዳ ፡፡ “ካልእ” ትርጉሙ ልዩ ሌላ እንጅ “ኅድረት” አይደለም መገናኛም የለውም ፡፡
==========================================
ካልዕ የሚለውን ኅድረት ብለው ከተረጎሙ በኋላ “አላ በዘተቀብዐ” የሚለውን “አላ በዘተሰብአ” በማለት ከላይ “ወከብረ” ብለው ከለወጡት ጋር የማይገጥም ቃልን አስቀምጠውታል ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስን የመከለሱ ሥራና ሤራ ተጧጡፎ ቀጥሏል!!
ግእዙ ክርስቶስ የተባለው በሌላ ነገር አይደለም ስለተቀባ ነው እንጅ ነው ትርጉሙ ፡፡ ከላይ ከመጀመሪያው ቃል ጀምሮ ስትመለከቱት ከአብ በሚገኝ ክብር ከበረ ፤ በመክበሩም ክርስቶስ ተባለ ፤ ክርስቶስ የተባለውም በሌላ አይደለም በመቀባቱ(በመክበሩ) ነው እንጅ አለ ፡፡ እሳቸው ግን ግማሹን ተቀብዐ ግማሹን ተሰብአ እያሉ አወላግደውታል ፤፤
===========================================
ይኸም ብቻ አይደለም አንባቢው ወገኔ!!!
ከላይ ተቀብዐ ማለትን ወደ ከብረ ለውጠውት የነበረውን ሙሉ በሙሉ አፍርሰው
“እስመ ክርስቶስ ብሂል ቅቡዕ ብሂል” የሚለውን ዋና ዘር “እስመ ክርስቶስ ብሂል አሐዱ እምክልኤቱ” ብለው ሙሉ በሙሉ ደመሰሱት ፡፡
በደንብ ተረዱት የሀሳቡ ሙሉ ትርጓሜ
“ከአብ በተገኘ ክብር ከብሯልና ክርስቶስ ተባለ ፤ ክርስቶስ የተባለውም በሌላ አይደለም ስለተቀባ ነው እንጅ ፡፡ ክርስቶስ ማለት የተቀባ ነውና” ማለት ነው ፤፡
አባ ዕዝራ ግን “ከአብ በተገኘ ክብር ከብሯልና ክርስቶስ ተባለ” የሚለውን ከተቀበሉ በኋላ ፤ “ክርስቶስ የተባለው ስለተቀባ ነው” የሚለውን ለውጠው “ክርስቶስ የተባለው ቢዋሐድ ነው” ብለው ተረጎሙት ፡፡ መነሻው ግን ስለከበረ ክርስቶስ ተባለ ነበር ፤ መድረሻው ላይ ሳይደርሱ “ስለተቀባ ነው” የሚለውን “ስለተዋሐደ ነው” ብለው ከመንገድ መለሱት ፤ ያመኑትንም ሙሉጭ አድርገው ካዱት ፡፡
ከዚያም “ክርስቶስ ማለት ቅቡዕ(የተቀባ) ማለት ነው” ብሎ ወገብ ዛላቸውን እንዳይላቸው ስለሰጉ “ቅቡዕ” የሚለውን ቀይረው “አሐዱ እምክልኤቱ” በማለት ያልተጻፈውን አምጥተው አስገቡበት ፡፡ እንግዲህ ዓይናችን ያያልና መጽሐፍ ቅዱስን እየቀየሩ እውነትን ማጥፋት እስከመቼ ይሆንላቸው ይሆን???
===========================================
በዚህ ነው የሚገርማችሁ
“አሐዱ እምክልኤቱ” የሚለውን “በተዋሕዶ ከበረ” ብለው አልተረጎሙትም መሰላችሁ!!!
አየህ ግእዝን የማይሰማ ትውልድ ተፈጠረላቸውን እንዲህ እያወላገዱ ይጭኑታል ፡፡
“አሐዱ እምክልኤቱ” ትርጉሙ “ከሁለቱ አንድ ሆነ” ማለት ነው ፡፡ ሁለቱም “ቃልና ሥጋ” ናቸው ፡፡
===========================================
የቄርሎስ ማጠንጠኛ ግን ከአብ በሚገኝ ቅብዓት ተቀብቷልና ክርስቶስ ተባለ ነው ፡፡
ተቀብዐን አመልጥ አመልጥ ቢሮጡ መዳረሻው ምንታዌ ነው ፤ ማምለጥ የለም ፡፡ ተቀብዐን መጽሐፍ ቅዱስን ማደስ ግስ መቀየር ፤ መጽሐፍ ቅዱስን መሰረዝ መደለዝ የአረሚነት የከሐዲነት ግብር ነው እንጅ የኦርቶዶክሰዊነት ግብር አይደለም ፡፡ መጻሕፍትን ለሚቆነጻጽሉት አምላክ ልቡና ይስጣቸው ፡፡ ለተሳዳቢዎችም ዓይናቸውን ያብራላቸው ፡፡ ለእኛም በሃይማኖት መጽናትን ፤ እድሜ ለንሥሃ ዘመን ለፍሥሐ ያድለን አሜን!
ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ!!
የብራናው ቃል በፎቶ ይኸው
ይኸንንም እያየ ዓይኔን ግንባር የሚል ዘላን እንደማይታጣም አብራችሁ ታዘቡልኝ!!!
