“ጽንዓ ተዋሕዶ ወይስ ጽንዓ ምንታዌ”
ክፍል አንድ
ሰሞኑን በሳምባ ምች ምክንያት ጋደም ብየ አንድ መጽሐፍ እያነበብኩ እገኛለሁ ፡፡ የመጽሐፉ ርዕስ “ጽንዓ ተዋሕዶ” ይባላል ፡፡ በአማን ነጸረ በሚባል ጸሐፊ ሰኔ 2012 ዓ.ም የታተመ መጽሐፍ እንደሆነ ከመግቢያው ይናገራል ፡፡
የመጽሐፉ ርዕስ መሢሐውያን አበው ከጻፉት ወልደ አብ ከተባለው ጉምቱ መጽሐፍ የተወሰደ ስም ነው -ጽንዓ ተዋሕዶ ፡፡ ሀሳቡ ተቀብዐ ተኮር ሐተታዎችንና ታሪኮችን ያነሳሳል ፡፡ ስሙ ደስ ብሎኝ ነበር ነገር ግን ያው እንደሌሎቹ “ተዋሕዶዎች” እነልዮንን እነ ንስጥሮስን በቃል እየነቀፈ በግብር እነሱን የደገፈ መጽሐፍ ሆኖ አግኝቸዋለሁ ፡፡