በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ-ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተላለፈ ቃለ-ግዘት!!!
እኛ በኢትዮጵያ(ጎጃም) የምንኖር ኦርቶዶክሳውያን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያንን ሕግና ሥርዓት ጠብቀንና አምነን መቆየታችን አሁንም እየጠበቅን የምንገኝ መሆናችን የሚታወስ ነው ፡፡ በዚህ ቆይታ ወደኋላ መለስ ብለን ስለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን ታሪካዊ ክስተት ብንመለከት የውጭ ሀገር ሚሲዮኖች ወደ ሐገራችን በመምጣታቸው በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ልዩ ችግር ተፈጠረ ፡፡ ሆድ አደር ሊቃውንትም አንዲት የቀናች መንገድን (ኦርቶዶክስን) በውጭ ጠላት ገንዘብና ሹመት ተደልለው፤በምፀት አነጋገርና በጥላቻ መንፈስ “ቅብዐት፣ ካራ፣ ፀጋ ፤ ሚናስ ፤ ፃማ” በመበባል እርስ በእርሳቸው ይነቃቀፉ እንደነበር የታሪክ መጻሕፍትን አገላብጦ መመልከት ይቻላል ፡፡