Tuesday, May 5, 2020
Sunday, May 3, 2020
የካራ ልጅ በአፍ የጦጣ ልጅ በዛፍ የቅብዓት ልጅ በመጽሐፍ!!!
ሃይማኖት መሢሐዊት!!!!!!!!!
የካራ ልጅ በአፍ የጦጣ ልጅ በዛፍ የቅብዓት ልጅ በመጽሐፍ!!!!
=================+=================ወዳጃችን እኛ እኮ ትግላችን እንዲሁ አይደለም ፡፡ የካራ ልጅ በአፍ የቅብዓት ልጅ በመጽሐፍ ስንልም እኮ በአሉ ይባላል በተረት ተረት አይደለም ከዚህ በታች እንደምንመለከተው ባለ ዓይነት ሽንጣም መጽሐፍ ነው እንጅ ፡፡ ሲያምኑ ግማሽ ሲተረጉሙ ዳሽ ማለታችንም እኮ ወደን አይደለም እንዲህ ከዚህ በታች እንደምትመለከቱት ግእዙ ከአማርኛው የማይስማማ የተደናበረ ትርጓሜን እየተረጎሙ ጠፍተው የሚያጠፉ የክፉ ልጆችን ግብር በማስረጃ እያቀረብን እንጅ ፡፡ መተርጉማን የሚሏቸው ከንቱ ሰዎች እንዲህ እያወላገዱ ሲተረጉሙት ስንመለከት ሲተረጉሙ ዳሽ አልናቸው ፤ መድኅን ክርስቶስ በመቀባቱ ክርስቶስ የተባለበትን ምሥጢር ትተው አማኑኤል የተባለባትን (ይህችንም ቢሆን ለሊሁ ቀባዒ ወተቀባዒ ወለሊሁ ቅብዕ ብለው ሲደናበሩ ቢያጠፏትም) ብቻ አንጠልጥለው ሲጓዙ ስናያቸው እና አማኑኤል አምላካችን በሰውነቱ የፈጸማቸውን ድንቅ ድንቅ ነገሮችን ለእነሱ የተመቻቸውን ብቻ እየመራረጡ ሲናገሩ ስንሰማቸው ሲያምኑ ግማሽ አልናቸው ፡፡ ታዲያ እንደ አባቶቻቸውና እንደ አያቶቻቸው እንደ አይሁድና ጸሐፍት ፈሪሳውያን ልቡናቸው የደነዘዘ በመሆኑ አሁንም ቢሆን የተሳሳቱ አልመሰላቸውም ፤ መጽሐፉ ግን “በእንተ ቅብዓት ተሰምየ ክርስቶስ” ሲተረጎም ስለ ቅብዓት ክርስቶስ ተባለ ፡፡ “እስመ ክርስቶስ ብሂል ቅቡዕ በመንፈስ ቅዱስ” ክርስቶስ ማለት በመንፈስ ቅዱስ የተቀባ የከበረ ማለት ነውና ይለናል ፡፡ በዘመኑ ትውልዱ ሁሉ ከልሳነ ግእዝ እልም ብሎ ስለራቀላቸው አፈ ቀላጤዎቹ “በእንተ ቅብዓት ተሰምየ ክርስቶስ” የሚለውን ሲተረጉሙ “ሥጋን ስለተዋሐደ ክርስቶስ ተባለ” ብለው የሌለ ፈጠራ የማይገናኝ ልብወለድን ይናገራሉ ፡፡ በግእዙ ላይ ሥጋ የሚል የለም ተዋሕዶም የሚል የለም እነሱ መጨማመር ልማዳቸው ነውና የጨማመሩት ነው ፡፡ ከዚያም በኋላ በምን ተቀባ ብለን ግራ እንዳይገባን “እስመ ክርስቶስ ብሂል ቅቡዕ
Subscribe to:
Posts (Atom)