Wednesday, March 6, 2019

ውሉደ ይሁዳ (ክፍል ሁለት)

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ  አምላክ አሜን!
==========================================
በባለፈው በክፍል አንድ መልእቴ “ዐራት ዓይናው” አባ “ሰሎሞን ዳዊት” “ቅባትን በእሳት” የምትል የጨዋ ንግግርን በተናሩባት ወቅት እሳትን በእሳት የሚል ሀሳብን ማንሳታቸውንና ዐራት ዓይናው አንድ ዓይና እንኳን የማያስብላቸውን ነገር መናገራቸውንና እንደይሁዳ አምላካቸው መንፈስ ቅዱስን እየሰደቡ በ30 ብር እየቸበቸቡ የሚገኙ መሆናቸውን በሐተታ አንስቼ መዘከሬ ይታወሳል ፡፡ እነሆ በቀጠሮየ መሠረት ዛሬ ደግሞ በመጽሐፏ ውስጥ ብዙውን ስፍራ የያዘው “ተዋሕዶ ሃይማኖታችን” የሚል ቃል አንስቼ እንድንወያይ አምላክ በፈቀደልን መጠን ይህችን ጽሁፍ እንካችሁ ብያለሁ፡፡