Thursday, February 28, 2019

ውሉደ ይሁዳ (ክፍል አንድ)

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ይድረስ  ለ “ሊቀ ሊቃውንት”  ሰሎሞን ዳዊት
===========================================
በ21ኛው መቶ ክፍለዘመን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን በምሥራቃዊት ጎጃም ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ሥር (መቀመጫውን ደብረ ማርቆስ ባደረገው) የዐራቱ ጉባዔ መምህር ተብለው የሚጠሩት መሪጌታ ሰሎሞን ዳዊት "ቅባትን በእሳት" የምትል ርእስ ያላት በዋጋዋ ክርስቶስን እንደሸጠ እንደይሁዳ መንፈስ ቅዱስን በ30 ብር የምትሸጥ መጽሐፍ ጽፈዋል ፡፡ እጅጉን የሚደንቀው ደግሞ ግሱንም ይሆን ከግሱ የሚወጣውን ሳቢ ዘር የማይለዩ ጨዋ ሰው ሁነው ሳገኛቸው ፤ ስማቸውና ማንነታቸው የማይገናኙ መሆናቸው የበለጠ ግልጽ ይሆናል ፡፡ “እሱም ቅባትን በእሳት” የሚል ነው ፡፡